መዝሙር 24
24
መዝሙር 24
የዳዊት መዝሙር።
1ምድርና በርሷ ያለው ሁሉ፣
ዓለምና በውስጧ የሚኖር ሁሉ የእግዚአብሔር ነው፤
2እርሱ በባሕሮች ላይ መሥርቷታልና፤
በውሆችም ላይ አጽንቷታል።
3ወደ እግዚአብሔር ተራራ ማን ሊወጣ ይችላል?
በተቀደሰ ስፍራውስ ማን ይቆማል?
4ንጹሕ እጅና ቅን ልብ ያለው፤
ነፍሱን ለሐሰት ነገር የማያስገዛ፤
በውሸት የማይምል።#24፥4 ወይም በሐሰትም ያልማለ
5እርሱ በረከትን ከእግዚአብሔር ዘንድ፣
ጽድቅንም ከአዳኝ አምላኩ ይቀበላል።
6እርሱን የሚፈልግ ትውልድ እንዲህ ነው፤
የያዕቆብ አምላክ ሆይ፤ ፊትህን#24፥6 ሁለት የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆችና ሱርስት (እንዲሁም ሰብዓ ሊቃናትን ይመ) እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን ያዕቆብ፤ ፊትህን… የሚፈልግ እንዲህ ያለ ነው። ሴላ
7እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤
እናንተ የዘላለም በሮች፤
የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!
8ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው?
እግዚአብሔር ነው ብርቱና ኀያል፤
እግዚአብሔር ነው በውጊያ ኀያል።
9እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤
እናንተ የዘላለም በሮች፤
የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!
10ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው?
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣
እርሱ የክብር ንጉሥ ነው። ሴላ
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 24
24
መዝሙር 24
የዳዊት መዝሙር።
1ምድርና በርሷ ያለው ሁሉ፣
ዓለምና በውስጧ የሚኖር ሁሉ የእግዚአብሔር ነው፤
2እርሱ በባሕሮች ላይ መሥርቷታልና፤
በውሆችም ላይ አጽንቷታል።
3ወደ እግዚአብሔር ተራራ ማን ሊወጣ ይችላል?
በተቀደሰ ስፍራውስ ማን ይቆማል?
4ንጹሕ እጅና ቅን ልብ ያለው፤
ነፍሱን ለሐሰት ነገር የማያስገዛ፤
በውሸት የማይምል።#24፥4 ወይም በሐሰትም ያልማለ
5እርሱ በረከትን ከእግዚአብሔር ዘንድ፣
ጽድቅንም ከአዳኝ አምላኩ ይቀበላል።
6እርሱን የሚፈልግ ትውልድ እንዲህ ነው፤
የያዕቆብ አምላክ ሆይ፤ ፊትህን#24፥6 ሁለት የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆችና ሱርስት (እንዲሁም ሰብዓ ሊቃናትን ይመ) እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን ያዕቆብ፤ ፊትህን… የሚፈልግ እንዲህ ያለ ነው። ሴላ
7እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤
እናንተ የዘላለም በሮች፤
የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!
8ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው?
እግዚአብሔር ነው ብርቱና ኀያል፤
እግዚአብሔር ነው በውጊያ ኀያል።
9እናንተ ደጆች፤ ቀና በሉ፤
እናንተ የዘላለም በሮች፤
የክብር ንጉሥ እንዲገባ ብድግ በሉ!
10ይህ የክብር ንጉሥ ማን ነው?
የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣
እርሱ የክብር ንጉሥ ነው። ሴላ
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.