መዝሙር 43
43
መዝሙር 43#43 በብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች መዝሙር 42 እና 43 አንድ መዝሙር ነው።
1አምላክ ሆይ፤ ፍረድልኝ፤
ካልታመኑህ ሕዝብ ጋራ ተሟገትልኝ፤
ከአታላዮችና ከክፉዎች ሰዎችም አድነኝ።
2አምላክ ሆይ፤ አንተ ብርታቴ ነህና፣
ለምን ተውኸኝ?
ጠላትስ እያስጨነቀኝ፣
ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ?
3ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤
እነርሱ ይምሩኝ፤
ወደ ተቀደሰው ተራራህ፣
ወደ ማደሪያህ ያድርሱኝ።
4እኔም ወደ እግዚአብሔር መሠዊያ አቀናለሁ፤
ፍጹም ደስታዬ ወደ ሆነው አምላክ እሄዳለሁ፤
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፣
በበገና አመሰግንሃለሁ።
5ነፍሴ ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ?
ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ?
ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ፤
አዳኜና አምላኬን፣
ገና አመሰግነዋለሁና።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.