መዝሙር 70
70
መዝሙር 70
70፥1-5 ተጓ ምብ – መዝ 40፥13-17
ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር፤ ለመታሰቢያ።
1አምላክ ሆይ፤ ታድነኝ ዘንድ ዘንበል በል፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
2ነፍሴን ለመንጠቅ የሚፈልጉ፣
ይፈሩ፤ ይዋረዱም፤ ጕዳቴንም የሚሹ፣
ተዋርደው በመጡበት ይመለሱ።
3በእኔ ላይ፣ “ዕሠይ! ዕሠይ!” የሚሉ፣
ተሸማቅቀው ወደ ኋላ ይመለሱ።
4አንተን የሚፈልጉ ሁሉ ግን፣
ሐሤት ያድርጉ፤ በአንተም ደስም ይበላቸው፤
ማዳንህን የሚወድዱ ሁሉ ሁልጊዜ
“እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል!” ይበሉ።
5እኔ ግን ችግረኛና ድኻ ነኝ፤
አምላክ ሆይ፤ ፈጥነህ ድረስልኝ፤
አንተ ረዳቴና፣ ታዳጊዬም ነህና፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ አትዘግይ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.