ትንቢተ ዳንኤል 11
11
1“እኔም በሜዶናዊው በዳርዮስ መጀመሪያ ዓመት አጸናውና አበረታው ዘንድ ቆሜ ነበር።
2“አሁንም እውነትን እነግርሃለሁ። እነሆ ሦስት ነገሥታት ደግሞ በፋርስ ይነሣሉ፤ አራተኛውም ከሁሉ ይልቅ እጅግ ባለጸጋ ይሆናል፤ በባለጸግነቱም በበረታ ጊዜ በግሪክ መንግሥት ላይ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በግሪኮች መንግሥታት ላይ” ይላል። ሁሉን ያስነሣል። 3ኀያልም ንጉሥ ይነሣል፤ ትልቅ አገዛዝንም ይገዛል፤ እንደ ፈቃዱም ያደርጋል። 4በተነሣም ጊዜ መንግሥቱ ትሰበራለች፤ በአራቱም ነፋሳት ትበተናለች፤ ለዘሩ ግን አይከፋፈልም፤ ከእርሱም በኋላ እርሱ እንደ ገዛበት አገዛዝ አይሆንም፤ መንግሥቱ ታልፋለች፤ ከእነዚህም ለሌሎች ትሰጣለች።
5“የአዜብም ንጉሥ ይበረታል፤ ከአለቆቹም አንዱ በእርሱ ላይ ይበረታል፤ ከእርሱም ይልቅ ብዙ ግዛትን ይገዛል። 6ከዘመናትም በኋላ ይቀላቀላሉ፤ የአዜብም ንጉሥ ሴት ልጅ ቃል ኪዳን ለማድረግ ወደ መስዕ ንጉሥ ትመጣለች። የክንድዋ ኀይል ግን አይጸናም፤ ዘሩም#ዕብ. “እርሱና ክንዱ” ይላል። አይጸናም፤ እርስዋና እርስዋን ያመጡ፥ የወለዳትም፥ በዚያም ዘመን ያጸናት አልፈው ይሰጣሉ።
7ነገር ግን ከሥርዋ ቍጥቋጥ አንዱ በስፍራው ይነሣል፤ ወደ ሠራዊቱም ይመጣል፤ ወደ መስዕም ንጉሥ አምባ ይገባል፤ በላያቸውም ያደርጋል፤ ያሸንፍማል። 8አማልክቶቻቸውንና ቀልጠው የተሠሩትን ምስሎቻቸውን ከብርና ከወርቅም የተሠሩትን የከበሩትን ዕቃዎች ወደ ግብፅ ይማርካል፤#ግእዝ “አለቆቻቸውን ከአማልክቶቻቸውና ከመኳንንቶቻቸው ከተወደደ ገንዘባቸው ሁሉ ጋር ያጠፋቸዋል ወርቃቸውና ብራቸውም በምርኮ ወደ ግብፅ ይወሰዳል” ይላል። እርሱም ከመስዕ ንጉሥ በላይ ሆኖ ይቆማል።#ዕብ. “እስከ ጥቂትም ዓመት ድረስ ከሰሜን ንጉሥ ጋር ሳይዋጋ ይቀመጣል” ይላል። 9ይህም ወደ አዜብ ንጉሥ መንግሥት ይገባል፥ ነገር ግን ወደ ገዛ ምድሩ ይመለሳል።
10“ልጆቹም ይዋጋሉ፤ ብዙ ሕዝብንና ሠራዊትን ይሰበስባሉ፤ እርሱም ይመጣል፤ ይበረታማል፤ ያልፍማል፤ ተመልሶም እስከ አምባው ድረስ ይዋጋል። 11የአዜብም ንጉሥ ይቈጣል፤ ወጥቶም ከመስዕ ንጉሥ ጋር ይዋጋል፤ ብዙ ሕዝብንም ለሰልፍ ያቆማል፤ ሕዝቡም አልፎ በእጁ ይሰጣል። 12ሕዝቡንም ይወስዳል፤ ልቡንም ያስታብያል፤ አእላፋትንም ይጥላል፤ ነገር ግን አያሸንፍም። 13የመስዕም ንጉሥ ይመለሳል፥ ከቀደመውም የበለጠ ብዙ ሕዝብን ያቆማል፤ በዘመናትና በዓመታትም ፍጻሜ ከታላቅ ሠራዊትና ከብዙ ሀብት ጋር ይመጣል። 14በዚያም ዘመን ብዙ ሰዎች በአዜብ ንጉሥ ላይ ይነሣሉ፤ ከሕዝብህም መካከል የዐመፅ ልጆች ራእዩን ያጸኑ ዘንድ ይነሣሉ፤ ነገር ግን ይወድቃሉ። 15የመስዕም ንጉሥ ይመጣል፤ አፈርንም ይደለድላል፤ የተመሸገችንም ከተማ ይይዛል፤ የአዜብም ክንድ የተመረጡትም ሕዝብ አይቆሙም፤ ለመቋቋምም ኀይል የላቸውም። 16ወደ እርሱ የሚመጣው እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ በፊቱም የሚቆም የለም፤ በመልካሚቱም ምድር ይቆማል፤ ሁሉም በእጁ ይፈጸማል። 17ከመንግሥቱም ሁሉ ኀይል ጋር ይመጣ ዘንድ ፊቱን ያቀናል፤ ከእርሱም ጋር አንድነትን ያደርጋል፤ ለጥፋቱም ሴት ልጅ ትሰጠዋለች፤ እርስዋም አትጸናም፤ ለእርሱም አትሆንም። 18ከዚህም በኋላ ፊቱን ወደ ደሴቶች ይመልሳል፤ ብዙዎችንም ይወስዳል፤ የኀፍረት አለቆቹንም ይሽራል፤ ኀፍረቱም በላዩ ይመለሳል። 19ፊቱንም ወደ ገዛ ምድሩ አንባዎች ይመልሳል፤ ደክሞም ይወድቃል፤ አይገኝምም።
20“የመንግሥትን ሥልጣንና ክብር የሚሽር ይነሣል፤ በመንበሩም ይቀመጣል፤ ነገር ግን በቍጣም ሳይሆን፥ በጦርነትም ሳይሆን ከጥቂት ቀን በኋላ ይሰበራል።
ጨካኙ የሶርያ ንጉሥ
21በእርሱም ስፍራ የተጠቃ ሰው ይነሣል፤ የመንግሥቱንም ክብር አይሰጡትም፤ በቀስታ ይመጣል፤ መንግሥትንም በማታለል ይይዛል። 22የሚጐርፉ ተዋጊዎቹም ክንዶች ከፊቱ ይሰበራሉ፤ እርሱና የቃል ኪዳኑ አለቃም ይሰበራሉ። 23ከእርሱም ጋር ከተወዳጀ በኋላ ተንኰልን ያደርጋል፤ ከጥቂትም ሕዝብ ጋር ወጥቶ ይበረታል። 24በቀስታም ከሀገር ሁሉ ወደ ለመለመችው ክፍል ይገባል፤ አባቶቹና የአባቶቹ አባቶች ያላደረጉትንም ያደርጋል፤ ብዝበዛውንና ምርኮውን፥ ሀብቱንም በመካከላቸው ይበትናል፤ በምሽጎችም ላይ እስከ ጊዜው ድረስ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በግብፅ ላይ” የሚል ይጨምራል። ዐሳቡን ይፈጥራል። 25በታላቅም ሠራዊት ሆኖ ኀይሉንና ልቡን በአዜብ ንጉሥ ላይ ያስነሣል፤ የአዜብም ንጉሥ በታላቅና በብዙ ሠራዊት ይበረታል፤ ነገር ግን ዐሳብ በእርሱ ላይ ይፈጥራሉና አይጸናም። 26መብሉንም የሚበሉ ሰዎች ይሰብሩታል፤ ሠራዊቱም ይጐርፋል፤ ብዙዎችም ተገድለው ይወድቃሉ። 27እነዚህም ሁለት ነገሥታት በልባቸው ክፋትን ያደርጋሉ፤ በአንድ ገበታም ተቀምጠው ሐሰትን ይናገራሉ፤ ገና ጊዜው አልደረሰምና አይከናወንላቸውም።
28“ከብዙም ሀብት ጋር ወደ ምድሩ ይመለሳል፥ ልቡም በተቀደሰው ቃል ኪዳን ላይ ይሆናል፤ ፈቃዱንም ያደርጋል፥ ወደ ገዛ ምድሩም ይመለሳል። 29በተወሰነውም ጊዜ ይመለሳል፤ ወደ አዜብም ይመጣል፤ ነገር ግን የኋለኛው እንደ ፊተኛው አይሆንም። 30ጺም፥ ከይተምና ኔባእ በእርሱ ላይ ይመጣሉ#ዕብ. “የኪትም መርከቦች ይመጡበታል” ይላል። ስለዚህ አዝኖ#“ስለዚህ አዝኖ” የሚለው በግእዝ የለም። ይመለሳል፥ በቅዱሱም ቃል ኪዳን ላይ ይቈጣል፤ ፈቃዱንም ያደርጋል፤ ተመልሶም ቅዱሱን ቃል ኪዳን የተዉትን ሰዎች ይመለከታል። 31ዘሮችም ከእርሱ ይነሣሉ፤ ቤተ መቅደሱንም ያረክሳሉ፤ የዘወትሩንም መሥዋዕት ያስቀራሉ፤ የጥፋትንም ርኵሰት ያቆማሉ። 32ቃል ኪዳኑን የሚበድሉትንም በማታለል ያስታሉ፤ ነገር ግን አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ ይበረታሉ፤ ያደርጋሉም። 33በሕዝቡም መካከል ያሉ ጥበበኞች ብዙ ሰዎችን ያስተምራሉ፤ ነገር ግን በሰይፍና በእሳት ነበልባል በምርኮና በብዙ ዘመን ብዝበዛ ይደክማሉ። 34በመከራም ጊዜ በጥቂት ርዳታ ይረዳሉ፤ ብዙ ሰዎችም በግብዝነት ወደ እነርሱ ይጨመራሉ። 35ጊዜው ገና አልደረሰምና ያግሏቸው፥ ያነጿቸውና ያጠሯቸው ዘንድ ከዐዋቂዎች እኩሌቶቹ እስከ ጊዜው ድረስ መከራ ይቀበላሉ፤ በከበረ ቦታ የሚቆም፥ መጽሐፍንም የሚያነብብ ሰው ይህን ነገር ልብ ያድርግ።#ምዕ. 11 ቍ. 35 በዕብ. እና በግሪክ ሰባ. ሊ. አጭር ነው።
36“ንጉሡም እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ ራሱንም ከፍ ከፍ ያደርጋል፤ በአማልክት ሁሉ ላይ ራሱን ታላቅ ያደርጋል፤ በአማልክትም አምላክ ላይ በትዕቢት ይናገራል፤ ቍጣም እስኪፈጸም ድረስ ይከናወንለታል፤ የተወሰነው ይደረጋልና። 37የአባቶቹንም አምላክ፥ የሴቶችንም ምኞት አያከብርም፤ ራሱንም በሁሉ ላይ ታላቅ ያደርጋልና አማልክትን ሁሉ አያውቅም። 38ጽኑዕ በሆነ በእግዚአብሔር ሥልጣንም ይኰራል፤#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “በእነዚህ ፋንታ ግን የአምባዎቹን አምላክ ያከብራል” ይላል። አባቶቹም ያላወቁትን አምላክ በወርቅና በብር፥ በዕንቍና በከበረ ነገር ያከብረዋል። 39ከባዕድም አምላክ ጋር የተመሸጉ ጽኑ አምባዎችን ያደርጋል፤ ክብርን ያበዛላቸዋል፤ በብዙም ላይ ያስገዛቸዋል፤ ምድርንም በዋጋ ይከፍላል።
40“በፍጻሜ ዘመንም የዐዜብ ንጉሥ ከእርሱ ጋር ይዋጋል፤ የመስዕም ንጉሥ ከሠረገሎችና ከፈረሰኞች፥ ከብዙ መርከቦችም ጋር ይመጣበታል፤ ወደ ሀገሮችም ይገባል፤ ይጐርፍማል፥#“ይጐርፍማል” የሚለው በዕብ. ብቻ። ያልፍማል። 41ወደ መልካሚቱም ምድር ይገባል፤ ብዙ ሀገሮችም ይወድቃሉ፤ ነገር ግን ኤዶምያስና ሞዓብ፥ ከአሞንም ልጆች የበለጡት ከእጁ ይድናሉ። 42እጁን በሀገሮች ላይ ይዘረጋል፤ የግብፅም ምድር ከእጁ አታመልጥም። 43በወርቅና በብርም መዝገብ ላይ ፥ በከበረችም በግብፅ ዕቃ ሁሉ ላይ ይሠለጥናል፤ የሊብያና#ግእዝ “የኖብያና” ይላል። የኢትዮጵያ ሰዎችም ረዳቶች ይሆኑታል። 44ከምሥራቅና ከሰሜን ግን ወሬ ይደርሰዋል፤ ይቸኩላልም፤ ብዙ ሰዎችንም ይገድልና ፈጽሞ ያጠፋ ዘንድ በታላቅ ቍጣ ይወጣል። 45ንጉሣዊ ድንኳኑንም በባሕርና በከበረው በቅዱሱ ተራራ መካከል ይተክላል፤ እስከ ጊዜውም ይበረታል። የሚረዳውም የለም።
Currently Selected:
ትንቢተ ዳንኤል 11: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fam.png&w=128&q=75)
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
ትንቢተ ዳንኤል 11
11
1“እኔም በሜዶናዊው በዳርዮስ መጀመሪያ ዓመት አጸናውና አበረታው ዘንድ ቆሜ ነበር።
2“አሁንም እውነትን እነግርሃለሁ። እነሆ ሦስት ነገሥታት ደግሞ በፋርስ ይነሣሉ፤ አራተኛውም ከሁሉ ይልቅ እጅግ ባለጸጋ ይሆናል፤ በባለጸግነቱም በበረታ ጊዜ በግሪክ መንግሥት ላይ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በግሪኮች መንግሥታት ላይ” ይላል። ሁሉን ያስነሣል። 3ኀያልም ንጉሥ ይነሣል፤ ትልቅ አገዛዝንም ይገዛል፤ እንደ ፈቃዱም ያደርጋል። 4በተነሣም ጊዜ መንግሥቱ ትሰበራለች፤ በአራቱም ነፋሳት ትበተናለች፤ ለዘሩ ግን አይከፋፈልም፤ ከእርሱም በኋላ እርሱ እንደ ገዛበት አገዛዝ አይሆንም፤ መንግሥቱ ታልፋለች፤ ከእነዚህም ለሌሎች ትሰጣለች።
5“የአዜብም ንጉሥ ይበረታል፤ ከአለቆቹም አንዱ በእርሱ ላይ ይበረታል፤ ከእርሱም ይልቅ ብዙ ግዛትን ይገዛል። 6ከዘመናትም በኋላ ይቀላቀላሉ፤ የአዜብም ንጉሥ ሴት ልጅ ቃል ኪዳን ለማድረግ ወደ መስዕ ንጉሥ ትመጣለች። የክንድዋ ኀይል ግን አይጸናም፤ ዘሩም#ዕብ. “እርሱና ክንዱ” ይላል። አይጸናም፤ እርስዋና እርስዋን ያመጡ፥ የወለዳትም፥ በዚያም ዘመን ያጸናት አልፈው ይሰጣሉ።
7ነገር ግን ከሥርዋ ቍጥቋጥ አንዱ በስፍራው ይነሣል፤ ወደ ሠራዊቱም ይመጣል፤ ወደ መስዕም ንጉሥ አምባ ይገባል፤ በላያቸውም ያደርጋል፤ ያሸንፍማል። 8አማልክቶቻቸውንና ቀልጠው የተሠሩትን ምስሎቻቸውን ከብርና ከወርቅም የተሠሩትን የከበሩትን ዕቃዎች ወደ ግብፅ ይማርካል፤#ግእዝ “አለቆቻቸውን ከአማልክቶቻቸውና ከመኳንንቶቻቸው ከተወደደ ገንዘባቸው ሁሉ ጋር ያጠፋቸዋል ወርቃቸውና ብራቸውም በምርኮ ወደ ግብፅ ይወሰዳል” ይላል። እርሱም ከመስዕ ንጉሥ በላይ ሆኖ ይቆማል።#ዕብ. “እስከ ጥቂትም ዓመት ድረስ ከሰሜን ንጉሥ ጋር ሳይዋጋ ይቀመጣል” ይላል። 9ይህም ወደ አዜብ ንጉሥ መንግሥት ይገባል፥ ነገር ግን ወደ ገዛ ምድሩ ይመለሳል።
10“ልጆቹም ይዋጋሉ፤ ብዙ ሕዝብንና ሠራዊትን ይሰበስባሉ፤ እርሱም ይመጣል፤ ይበረታማል፤ ያልፍማል፤ ተመልሶም እስከ አምባው ድረስ ይዋጋል። 11የአዜብም ንጉሥ ይቈጣል፤ ወጥቶም ከመስዕ ንጉሥ ጋር ይዋጋል፤ ብዙ ሕዝብንም ለሰልፍ ያቆማል፤ ሕዝቡም አልፎ በእጁ ይሰጣል። 12ሕዝቡንም ይወስዳል፤ ልቡንም ያስታብያል፤ አእላፋትንም ይጥላል፤ ነገር ግን አያሸንፍም። 13የመስዕም ንጉሥ ይመለሳል፥ ከቀደመውም የበለጠ ብዙ ሕዝብን ያቆማል፤ በዘመናትና በዓመታትም ፍጻሜ ከታላቅ ሠራዊትና ከብዙ ሀብት ጋር ይመጣል። 14በዚያም ዘመን ብዙ ሰዎች በአዜብ ንጉሥ ላይ ይነሣሉ፤ ከሕዝብህም መካከል የዐመፅ ልጆች ራእዩን ያጸኑ ዘንድ ይነሣሉ፤ ነገር ግን ይወድቃሉ። 15የመስዕም ንጉሥ ይመጣል፤ አፈርንም ይደለድላል፤ የተመሸገችንም ከተማ ይይዛል፤ የአዜብም ክንድ የተመረጡትም ሕዝብ አይቆሙም፤ ለመቋቋምም ኀይል የላቸውም። 16ወደ እርሱ የሚመጣው እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ በፊቱም የሚቆም የለም፤ በመልካሚቱም ምድር ይቆማል፤ ሁሉም በእጁ ይፈጸማል። 17ከመንግሥቱም ሁሉ ኀይል ጋር ይመጣ ዘንድ ፊቱን ያቀናል፤ ከእርሱም ጋር አንድነትን ያደርጋል፤ ለጥፋቱም ሴት ልጅ ትሰጠዋለች፤ እርስዋም አትጸናም፤ ለእርሱም አትሆንም። 18ከዚህም በኋላ ፊቱን ወደ ደሴቶች ይመልሳል፤ ብዙዎችንም ይወስዳል፤ የኀፍረት አለቆቹንም ይሽራል፤ ኀፍረቱም በላዩ ይመለሳል። 19ፊቱንም ወደ ገዛ ምድሩ አንባዎች ይመልሳል፤ ደክሞም ይወድቃል፤ አይገኝምም።
20“የመንግሥትን ሥልጣንና ክብር የሚሽር ይነሣል፤ በመንበሩም ይቀመጣል፤ ነገር ግን በቍጣም ሳይሆን፥ በጦርነትም ሳይሆን ከጥቂት ቀን በኋላ ይሰበራል።
ጨካኙ የሶርያ ንጉሥ
21በእርሱም ስፍራ የተጠቃ ሰው ይነሣል፤ የመንግሥቱንም ክብር አይሰጡትም፤ በቀስታ ይመጣል፤ መንግሥትንም በማታለል ይይዛል። 22የሚጐርፉ ተዋጊዎቹም ክንዶች ከፊቱ ይሰበራሉ፤ እርሱና የቃል ኪዳኑ አለቃም ይሰበራሉ። 23ከእርሱም ጋር ከተወዳጀ በኋላ ተንኰልን ያደርጋል፤ ከጥቂትም ሕዝብ ጋር ወጥቶ ይበረታል። 24በቀስታም ከሀገር ሁሉ ወደ ለመለመችው ክፍል ይገባል፤ አባቶቹና የአባቶቹ አባቶች ያላደረጉትንም ያደርጋል፤ ብዝበዛውንና ምርኮውን፥ ሀብቱንም በመካከላቸው ይበትናል፤ በምሽጎችም ላይ እስከ ጊዜው ድረስ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በግብፅ ላይ” የሚል ይጨምራል። ዐሳቡን ይፈጥራል። 25በታላቅም ሠራዊት ሆኖ ኀይሉንና ልቡን በአዜብ ንጉሥ ላይ ያስነሣል፤ የአዜብም ንጉሥ በታላቅና በብዙ ሠራዊት ይበረታል፤ ነገር ግን ዐሳብ በእርሱ ላይ ይፈጥራሉና አይጸናም። 26መብሉንም የሚበሉ ሰዎች ይሰብሩታል፤ ሠራዊቱም ይጐርፋል፤ ብዙዎችም ተገድለው ይወድቃሉ። 27እነዚህም ሁለት ነገሥታት በልባቸው ክፋትን ያደርጋሉ፤ በአንድ ገበታም ተቀምጠው ሐሰትን ይናገራሉ፤ ገና ጊዜው አልደረሰምና አይከናወንላቸውም።
28“ከብዙም ሀብት ጋር ወደ ምድሩ ይመለሳል፥ ልቡም በተቀደሰው ቃል ኪዳን ላይ ይሆናል፤ ፈቃዱንም ያደርጋል፥ ወደ ገዛ ምድሩም ይመለሳል። 29በተወሰነውም ጊዜ ይመለሳል፤ ወደ አዜብም ይመጣል፤ ነገር ግን የኋለኛው እንደ ፊተኛው አይሆንም። 30ጺም፥ ከይተምና ኔባእ በእርሱ ላይ ይመጣሉ#ዕብ. “የኪትም መርከቦች ይመጡበታል” ይላል። ስለዚህ አዝኖ#“ስለዚህ አዝኖ” የሚለው በግእዝ የለም። ይመለሳል፥ በቅዱሱም ቃል ኪዳን ላይ ይቈጣል፤ ፈቃዱንም ያደርጋል፤ ተመልሶም ቅዱሱን ቃል ኪዳን የተዉትን ሰዎች ይመለከታል። 31ዘሮችም ከእርሱ ይነሣሉ፤ ቤተ መቅደሱንም ያረክሳሉ፤ የዘወትሩንም መሥዋዕት ያስቀራሉ፤ የጥፋትንም ርኵሰት ያቆማሉ። 32ቃል ኪዳኑን የሚበድሉትንም በማታለል ያስታሉ፤ ነገር ግን አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ ይበረታሉ፤ ያደርጋሉም። 33በሕዝቡም መካከል ያሉ ጥበበኞች ብዙ ሰዎችን ያስተምራሉ፤ ነገር ግን በሰይፍና በእሳት ነበልባል በምርኮና በብዙ ዘመን ብዝበዛ ይደክማሉ። 34በመከራም ጊዜ በጥቂት ርዳታ ይረዳሉ፤ ብዙ ሰዎችም በግብዝነት ወደ እነርሱ ይጨመራሉ። 35ጊዜው ገና አልደረሰምና ያግሏቸው፥ ያነጿቸውና ያጠሯቸው ዘንድ ከዐዋቂዎች እኩሌቶቹ እስከ ጊዜው ድረስ መከራ ይቀበላሉ፤ በከበረ ቦታ የሚቆም፥ መጽሐፍንም የሚያነብብ ሰው ይህን ነገር ልብ ያድርግ።#ምዕ. 11 ቍ. 35 በዕብ. እና በግሪክ ሰባ. ሊ. አጭር ነው።
36“ንጉሡም እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ ራሱንም ከፍ ከፍ ያደርጋል፤ በአማልክት ሁሉ ላይ ራሱን ታላቅ ያደርጋል፤ በአማልክትም አምላክ ላይ በትዕቢት ይናገራል፤ ቍጣም እስኪፈጸም ድረስ ይከናወንለታል፤ የተወሰነው ይደረጋልና። 37የአባቶቹንም አምላክ፥ የሴቶችንም ምኞት አያከብርም፤ ራሱንም በሁሉ ላይ ታላቅ ያደርጋልና አማልክትን ሁሉ አያውቅም። 38ጽኑዕ በሆነ በእግዚአብሔር ሥልጣንም ይኰራል፤#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “በእነዚህ ፋንታ ግን የአምባዎቹን አምላክ ያከብራል” ይላል። አባቶቹም ያላወቁትን አምላክ በወርቅና በብር፥ በዕንቍና በከበረ ነገር ያከብረዋል። 39ከባዕድም አምላክ ጋር የተመሸጉ ጽኑ አምባዎችን ያደርጋል፤ ክብርን ያበዛላቸዋል፤ በብዙም ላይ ያስገዛቸዋል፤ ምድርንም በዋጋ ይከፍላል።
40“በፍጻሜ ዘመንም የዐዜብ ንጉሥ ከእርሱ ጋር ይዋጋል፤ የመስዕም ንጉሥ ከሠረገሎችና ከፈረሰኞች፥ ከብዙ መርከቦችም ጋር ይመጣበታል፤ ወደ ሀገሮችም ይገባል፤ ይጐርፍማል፥#“ይጐርፍማል” የሚለው በዕብ. ብቻ። ያልፍማል። 41ወደ መልካሚቱም ምድር ይገባል፤ ብዙ ሀገሮችም ይወድቃሉ፤ ነገር ግን ኤዶምያስና ሞዓብ፥ ከአሞንም ልጆች የበለጡት ከእጁ ይድናሉ። 42እጁን በሀገሮች ላይ ይዘረጋል፤ የግብፅም ምድር ከእጁ አታመልጥም። 43በወርቅና በብርም መዝገብ ላይ ፥ በከበረችም በግብፅ ዕቃ ሁሉ ላይ ይሠለጥናል፤ የሊብያና#ግእዝ “የኖብያና” ይላል። የኢትዮጵያ ሰዎችም ረዳቶች ይሆኑታል። 44ከምሥራቅና ከሰሜን ግን ወሬ ይደርሰዋል፤ ይቸኩላልም፤ ብዙ ሰዎችንም ይገድልና ፈጽሞ ያጠፋ ዘንድ በታላቅ ቍጣ ይወጣል። 45ንጉሣዊ ድንኳኑንም በባሕርና በከበረው በቅዱሱ ተራራ መካከል ይተክላል፤ እስከ ጊዜውም ይበረታል። የሚረዳውም የለም።