ትን​ቢተ ዳን​ኤል 7

7
ስለ 4 አራ​ዊት ራእይ
1በባ​ቢ​ሎን ንጉሥ በብ​ል​ጣ​ሶር በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመተ መን​ግ​ሥት ዳን​ኤል በአ​ል​ጋው ላይ ሕል​ም​ንና የራ​ሱን ራእይ አየ፤ ከዚ​ያም በኋላ ሕል​ሙን ጻፈ፥ 2እን​ዲ​ህም አለ፥ “እኔ ዳን​ኤል ራእይ አየሁ፤ እነ​ሆም አራቱ የሰ​ማይ ነፋ​ሳት በታ​ላቁ ባሕር ላይ ይነ​ፍሱ ነበር። 3አራ​ትም ታላ​ላቅ አራ​ዊት ከባ​ሕር ወጡ፥ እያ​ን​ዳ​ን​ዲ​ቱም ከሌ​ላ​ይቱ ልዩ ነበ​ረች። 4መጀ​መ​ሪ​ያ​ይቱ እንደ ሴት አን​በሳ ነበ​ረች፤ እንደ ንስ​ርም ክንፍ ነበ​ራት፤ ክን​ፎ​ች​ዋም ከእ​ር​ስዋ እስ​ኪ​ነ​ቀሉ ድረስ አይ ነበር፤ ከም​ድ​ርም ከፍ ከፍ አለች፤ እንደ ሰውም በእ​ግር ቆመች፤ የሰ​ውም ልብ ተሰ​ጣት። 5እነ​ሆም ሁለ​ተ​ኛ​ይቱ ድብ የም​ት​መ​ስል ሌላ አውሬ ነበ​ረች፤ በአ​ንድ ወገ​ንም ቆመች፤ ሦስ​ትም የጎ​ድን አጥ​ን​ቶች በአ​ፍዋ ውስጥ በጥ​ር​ሶ​ችዋ መካ​ከል ነበሩ፤ እን​ደ​ዚ​ህም፦ ተነ​ሥ​ተሽ እጅግ ሥጋ ብዪ አሏት። 6ከዚ​ህም በኋላ፥ እነሆ ነብር የም​ት​መ​ስል፥ በጀ​ር​ባ​ዋም ላይ አራት የወፍ ክን​ፎች የነ​በ​ሩ​አት፤ ሌላ አውሬ አየሁ፤ ለአ​ው​ሬ​ይ​ቱም አራት ራሶች ነበ​ሩ​አት፤ ሥል​ጣ​ንም ተሰ​ጣት። 7ከዚ​ህም በኋላ በሌ​ሊት ራእይ አየሁ፤ እነ​ሆም የም​ታ​ስ​ፈ​ራና የም​ታ​ስ​ደ​ነ​ግጥ፥ እጅ​ግም የበ​ረ​ታች፥ ታላ​ላ​ቅም የብ​ረት ጥር​ሶች የነ​በ​ሩ​አት አራ​ተኛ አውሬ ነበ​ረች፤ ትበ​ላና ታደ​ቅቅ ነበር፥ የቀ​ረ​ው​ንም በእ​ግ​ርዋ ትረ​ግጥ ነበር፤ ከእ​ር​ስ​ዋም በፊት ከነ​በ​ሩት አራ​ዊት ሁሉ የተ​ለ​የች ነበ​ረች፤ ዐሥር ቀን​ዶ​ችም ነበ​ሩ​አት። 8ቀን​ዶ​ች​ንም ተመ​ለ​ከ​ትሁ፤ እነ​ሆም፤ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ሌላ ትንሽ ቀንድ ወጣ፤ በፊ​ቱም ከቀ​ደ​ሙት ቀን​ዶች ሦስት ተነ​ቃ​ቀሉ፤ እነ​ሆም በዚያ በት​ንሹ ቀንድ እንደ ሰው ዐይ​ኖች የነ​በሩ ዐይ​ኖች፥ በት​ዕ​ቢ​ትም የሚ​ና​ገር አፍ ነበ​ሩ​በት።
9“ዙፋ​ኖ​ችም እስ​ኪ​ዘ​ረጉ ድረስ አየሁ፤ በዘ​መ​ናት የሸ​መ​ገ​ለ​ውም ተቀ​መጠ፤ ልብ​ሱም እንደ በረዶ ነጭ፥ የራ​ሱም ጠጕር እንደ ነጭ ሱፍ ነበረ፤ ዙፋ​ኑም የእ​ሳት ነበ​ል​ባል ነበረ፥ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮ​ቹም የሚ​ነ​ድድ እሳት ነበሩ። 10የእ​ሳ​ትም ፈሳሽ ከፊቱ ይፈ​ል​ቅና ይወጣ ነበር፤ ሺህ ጊዜ ሺህ የሆኑ ያገ​ለ​ግ​ሉት ነበር፤ እልፍ አእ​ላ​ፋ​ትም በፊቱ ቆመው ነበር፤ ለፍ​ር​ድም ተቀ​መጠ፤ መጻ​ሕ​ፍ​ት​ንም ገለጠ። 11የዚ​ያን ጊዜም ይህ ቀንድ ከተ​ና​ገ​ረው ነገር የተ​ነሣ አው​ሬው እስ​ኪ​ር​ቅና እስ​ኪ​ጠፋ ድረስ አየሁ፤ በእ​ሳ​ትም ያቃ​ጥ​ሉት ዘንድ ሰው​ነ​ቱን አሳ​ል​ፈው ሰጡት፤ 12ከቀ​ሩ​ትም አራ​ዊት ግዛ​ታ​ቸው ተወ​ሰደ፤ የሕ​ይ​ወ​ታ​ቸው ዘመን ግን እስከ ተወ​ሰነ ጊዜ ድረስ ረዘመ።
13“በሌ​ሊ​ትም ራእይ አየሁ፤ እነ​ሆም የሰው ልጅ የሚ​መ​ስል በሰ​ማይ ደመና መጣ፤ በዘ​መ​ና​ትም ወደ ሸመ​ገ​ለው ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀ​ረ​ቡት። 14ወገ​ኖ​ችና አሕ​ዛብ፥ በልዩ ልዩ ቋን​ቋም የሚ​ና​ገሩ ሁሉ ይገ​ዙ​ለት ዘንድ ግዛ​ትና ክብር፥ መን​ግ​ሥ​ትም ተሰ​ጠው፤ ግዛ​ቱም የማ​ያ​ልፍ የዘ​ለ​ዓ​ለም ግዛት ነው፥ መን​ግ​ሥ​ቱም የማ​ይ​ጠፋ ነው።
የሕ​ልሙ ፍች
15“እኔም ዳን​ኤል መን​ፈሴ ተን​ቀ​ጠ​ቀ​ጠ​ብኝ፤ ከራ​ሴም ራእይ የተ​ነሣ ልቤ ደነ​ገ​ጠ​ብኝ። 16በዚ​ያም ከቆ​ሙት ወደ አንዱ ቀርቤ ስለ​ዚህ ሁሉ እው​ነ​ቱን ጠየ​ቅ​ሁት፤ እር​ሱም ነገ​ረኝ፤ የነ​ገ​ሩ​ንም ፍቺ አስ​ታ​ወ​ቀኝ፥ እኔም ነገ​ሩን ተረ​ዳ​ሁት። 17እን​ዲ​ህም አለኝ፦ እነ​ዚህ ያየ​ሃ​ቸው አራቱ ታላ​ላቅ አራ​ዊት ከም​ድር የሚ​ነሡ አራት ነገ​ሥ​ታት ናቸው፤ ዳግ​መ​ኛም ይወ​ገ​ዳሉ። 18ነገር ግን መን​ግ​ሥት ለል​ዑሉ ቅዱ​ሳን ይመ​ለ​ሳል፤ የል​ዑሉ ቅዱ​ሳ​ንም መን​ግ​ሥ​ቱን ይወ​ስ​ዳሉ፤ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ዓለ​ምም መን​ግ​ሥ​ቱን ይወ​ር​ሳሉ። 19ከዚ​ህም በኋላ ከቀ​ሩት ሁሉ ተለ​ይታ እጅግ ስለ​ም​ታ​ስ​ፈ​ራው፥ ጥር​ሶ​ች​ዋም የብ​ረት፥ ጥፍ​ሮ​ች​ዋም የናስ ስለ ሆኑት፥ ስለ​ም​ት​በ​ላ​ውና ስለ​ም​ታ​ደ​ቅ​ቀው፥ የቀ​ረ​ው​ንም በእ​ግ​ርዋ ስለ​ም​ት​ረ​ግ​ጠው ስለ አራ​ተ​ኛ​ዪቱ አውሬ፥ 20በራ​ስ​ዋም ላይ ስለ ነበሩ ስለ ዐሥር ቀን​ዶች፥ በኋ​ላም ስለ ወጣው፥ በፊ​ቱም ስለ ወደቁ ሦስቱ ቀን​ዶች፥ ዐይ​ኖ​ችና ትዕ​ቢት የተ​ና​ገረ አፍ ስለ ነበ​ሩት ራሱም ከሌ​ሎች ስለ በለጠ ስለ ሌላው ቀንድ እው​ነ​ቱን ለማ​ወቅ ጠየ​ቅ​ሁት። 21እነ​ሆም፥ ያ ቀንድ ከቅ​ዱ​ሳን ጋር ሲዋጋ አየሁ፤ አሸ​ነ​ፋ​ቸ​ውም፤ 22በዘ​መ​ናት የሸ​መ​ገ​ለው እስ​ኪ​መጣ ድረስ፥ ፍር​ድም ለል​ዑሉ ቅዱ​ሳን እስ​ኪ​ሰጥ ድረስ፥ ቅዱ​ሳ​ኑም መን​ግ​ሥ​ቱን የሚ​ወ​ስ​ዱ​በት ዘመን እስ​ኪ​መጣ ድረስ አሸ​ነ​ፋ​ቸው።
23“እን​ዲ​ህም አለኝ፦ አራ​ተ​ኛው አውሬ በም​ድር ላይ የሚ​ነሣ አራ​ተኛ መን​ግ​ሥት ነው፤ እር​ሱም ከመ​ን​ግ​ሥ​ታት ሁሉ ይበ​ል​ጣል።#ዕብ. “የተ​ለየ ይሆ​ናል” ይላል። ምድ​ሪ​ቱ​ንም ሁሉ ይበ​ላል፤ ይረ​ግ​ጣ​ታል፤ ያደ​ቅ​ቃ​ት​ማል። 24ዐሥ​ሩም ቀን​ዶች ከዚያ መን​ግ​ሥት የሚ​ነሡ ዐሥር ነገ​ሥ​ታት ናቸው፤ ከእ​ነ​ር​ሱም በኋላ ሌላ ይነ​ሣል፤ እር​ሱም ከፊ​ተ​ኞቹ በክ​ፋት የበ​ለጠ#ዕብ. “የተ​ለየ” ይላል። ይሆ​ናል፤ ሦስ​ቱ​ንም ነገ​ሥ​ታት ያዋ​ር​ዳል። 25በል​ዑ​ሉም ላይ ቃልን ይና​ገ​ራል፤ የል​ዑ​ል​ንም ቅዱ​ሳን ይሰ​ባ​ብ​ራል፤ ዘመ​ና​ት​ንና ሕግን ይለ​ውጥ ዘንድ ያስ​ባል፤ እስከ ዘመ​ንና እስከ ዘመ​ናት እስከ እኩ​ሌታ ዘመ​ንም በእጁ ይሰ​ጣሉ። 26ነገር ግን ፍርድ ይሆ​ናል፤ እስከ ፍጻ​ሜ​ውም ድረስ ያፈ​ር​ሱ​ትና ያጠ​ፉት ዘንድ ግዛ​ቱን ያስ​ወ​ግ​ዱ​ታል። 27መን​ግ​ሥ​ትም፥ ግዛ​ትም፥ ከሰ​ማ​ይም ሁሉ በታች ያሉ የመ​ን​ግ​ሥ​ታት ታላ​ቅ​ነት ለል​ዑሉ ቅዱ​ሳን ሕዝብ ይሰ​ጣል፤ መን​ግ​ሥቱ የዘ​ለ​ዓ​ለም መን​ግ​ሥት ነው፤ መኳ​ን​ን​ቱም ሁሉ ይገ​ዙ​ለ​ታል፤ ይታ​ዘ​ዙ​ለ​ት​ማል።” 28የነ​ገ​ሩም ፍጻሜ እስ​ከ​ዚህ ድረስ ነው። እኔም ዳን​ኤል በአ​ሳቤ እጅግ ተቸ​ገ​ርሁ፤ ፊቴም ተለ​ወ​ጠ​ብኝ፤ ዳሩ ግን ነገ​ሩን በልቤ ጠብ​ቄ​አ​ለሁ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ