ትን​ቢተ ሕዝ​ቅ​ኤል 10

10
የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብር ከቤተ መቅ​ደስ እንደ ተነሣ
1እኔም አየሁ፤ እነ​ሆም በኪ​ሩ​ቤል ራስ ላይ ባለው ጠፈር በላ​ያ​ቸው እንደ ሰን​ፔር ድን​ጋይ ያለ ዙፋን የሚ​መ​ስል መልክ ተገ​ለጠ። 2በፍ​ታም የለ​በ​ሰ​ውን ሰው፥ “በመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ሮች መካ​ከል በኪ​ሩብ በታች ግባ፤ ከኪ​ሩ​ቤ​ልም መካ​ከል ከአ​ለው እሳት ፍም እጆ​ች​ህን ሙላ፤ በከ​ተ​ማ​ዪ​ቱም ላይ በት​ነው” ብሎ ተና​ገ​ረው። እኔም እያ​የሁ ገባ። 3ሰው​የ​ውም ሲገባ ኪሩ​ቤል በቤቱ ቀኝ በኩል ቆመው ነበር፤ ደመ​ና​ውም ውስ​ጠ​ኛ​ውን አደ​ባ​ባይ ሞላ። 4የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብ​ርም ከኪ​ሩ​ቤል ወጥቶ በቤቱ መድ​ረክ ላይ ቆመ፤ ቤቱም በደ​መ​ናው ተሞላ፤ አደ​ባ​ባ​ዩም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብር ፀዳል ተሞላ። 5የኪ​ሩ​ቤ​ልም የክ​ን​ፎ​ቻ​ቸው ድምፅ ሁሉን የሚ​ችል አም​ላክ እን​ደ​ሚ​ና​ገ​ረው ያለ ድምፅ እስከ ውጭው አደ​ባ​ባይ ድረስ በሩቅ ይሰማ ነበር። 6የተ​ቀ​ደሰ በፍ​ታም የለ​በ​ሰ​ውን ሰው፥ “ከመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ ከኪ​ሩ​ቤል መካ​ከል እሳት ውሰድ” ብሎ በአ​ዘ​ዘው ጊዜ እርሱ ገብቶ በመ​ን​ኰ​ራ​ኵር አጠ​ገብ ቆመ። 7ከኪ​ሩ​ቤል መካ​ከ​ልም አንዱ ኪሩብ እጁን በኪ​ሩ​ቤል መካ​ከል ወደ አለው እሳት ዘር​ግቶ ከዚያ እሳት ወሰደ፤ የተ​ቀ​ደሰ በፍ​ታም በለ​በ​ሰው ሰው እጅ አኖ​ረው፤ እር​ሱም ይዞ ወጣ። 8ኪሩ​ቤ​ል​ንም አየሁ፤ ከክ​ን​ፎ​ቻ​ቸ​ውም በታች የሰው እጅ መሳይ አለ።
9እኔም አየሁ፤ እነ​ሆም በኪ​ሩ​ቤል አጠ​ገብ አራት መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮች ነበሩ፤ አንዱ መን​ኰ​ራ​ኵር በአ​ንዱ ኪሩብ፥ አንዱ መን​ኰ​ራ​ኵር በአ​ንዱ ኪሩብ አጠ​ገብ ነበረ። የመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ሮ​ቹም መልክ እንደ ቢረሌ ድን​ጋይ ነበረ። 10የአ​ራ​ቱም መልክ አንድ ይመ​ስል ነበር፤ መል​ካ​ቸ​ውም በመ​ን​ኰ​ራ​ኵር ውስጥ እንደ አለ መን​ኰ​ራ​ኵር ነበረ። 11ሲሔ​ዱም በአ​ራቱ ጎድ​ና​ቸው ይሄዱ ነበር። ሲሄ​ዱም ወዲ​ያና ወዲህ አይ​ሉም ነበር፤ መጀ​መ​ሪ​ያው ወደ​ሚ​ያ​መ​ለ​ክ​ት​በት ስፍራ ይሄዱ ነበር፤ ሲሄ​ዱም ወዲ​ያና ወዲህ አይ​ሉም ነበር። 12ገላ​ቸ​ውም ሁሉ፥ ጀር​ባ​ቸ​ውም፥ እጆ​ቻ​ቸ​ውም፤ ክን​ፎ​ቻ​ቸ​ውም፥ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮ​ቹም፤ ለአ​ራቱ የነ​በሩ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮች በዙ​ሪ​ያ​ቸው ዐይ​ኖች ተሞ​ል​ተው ነበር። 13አራ​ቱም መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮች እኔ እየ​ሰ​ማሁ ጌል​ጌል ተብ​ለው ተጠሩ። 14ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም አራት አራት ፊት ነበ​ሩት፤ አን​ደ​ኛው ፊት የኪ​ሩብ#“ገጸ ኪሩብ” የተ​ባለ ገጸ ላሕም ነው። ፊት፥ ሁለ​ተ​ኛ​ውም የሰው ፊት፥ ሦስ​ተ​ኛው የአ​ን​በሳ ፊት፥ አራ​ተ​ኛ​ውም የን​ስር ፊት ነበረ።#ምዕ. 10 ቍ. 14 በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም።
15እነ​ዚ​ህም በኮ​ቦር ወንዝ በእ​ን​ስ​ሶች አም​ሳል ያየ​ኋ​ቸው ኪሩ​ቤል በረሩ። 16ኪሩ​ቤ​ልም ሲሄዱ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ተያ​ይ​ዘው ይሄዱ ነበር፤ ኪሩ​ቤ​ልም ይበሩ ዘንድ ክን​ፋ​ቸ​ውን ከም​ድር በሚ​ያ​ነሡ ጊዜ ከእ​ነ​ርሱ ጋር የተ​ያ​ያዘ መን​ኰ​ራ​ኵ​ራ​ቸው አይ​መ​ለ​ስም ነበር። 17የሕ​ይ​ወት መን​ፈስ በው​ስ​ጣ​ቸው ነበ​ርና እነ​ዚህ ሲቆሙ እነ​ዚ​ያም ይቆሙ ነበር፤ እነ​ዚ​ህም ሲበ​ርሩ፥ እነ​ዚያ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ይበ​ርሩ ነበር።
18የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ክብር ከቤቱ መድ​ረክ ላይ ወጥቶ በኪ​ሩ​ቤል ላይ ተቀ​መጠ። 19ኪሩ​ቤ​ልም ክን​ፎ​ቻ​ቸ​ውን ዘረጉ፤ እኔም እያ​የሁ ከም​ድር በረሩ፤ በወ​ጡም ጊዜ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ በአ​ጠ​ገ​ባ​ቸው ነበሩ፤ፊት ለፊት በአ​ለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት መግ​ቢያ በር ዳርቻ ቆሙ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም አም​ላክ ክብር ከእ​ነ​ርሱ ጋራ በላ​ያ​ቸው ነበረ።
20ይህ በኮ​ቦር ወንዝ ከእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በታች ያየ​ሁት እን​ስሳ ነው፤ ኪሩ​ቤ​ልም እንደ ነበሩ ዐወ​ቅሁ። 21ለእ​ያ​ን​ዳ​ንዱ አራት አራት ፊት፥ ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም አራት አራት ክንፍ ነበ​ሩት፤ የሰ​ውም እጅ አም​ሳያ ከክ​ን​ፎ​ቻ​ቸው በታች ነበረ። 22ፊቶ​ቻ​ቸ​ውም በኮ​ቦር ወንዝ ከእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ክብር በታች ያየ​ኋ​ቸ​ውን ፊቶች ይመ​ስሉ ነበር፤ እነ​ር​ሱና መል​ካ​ቸ​ውም እን​ዲሁ ነበረ፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዱም አቅ​ንቶ ወደ ፊት ይሄድ ነበር።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ