መዝሙረ ዳዊት 92
92
በሰንበት ቀን የምስጋና መዝሙር።
1እግዚአብሔር ነገሠ፥ ክብሩንም ለበሰ፤
እግዚአብሔር ኀይልን ለበሰ፥ ታጠቀም፤
ዓለምንም እንዳትናወጥ አጸናት።
2አቤቱ፥#“አቤቱ” የሚለው በግእዝ ብቻ። ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የተዘጋጀ ነው፥
አንተም መቼም መች እስከ ዘለዓለም ነህ።
3አቤቱ፥ ወንዞች ከፍ ከፍ አደረጉ፥
ወንዞች ቃሎቻቸውን ከፍ ከፍ አደረጉ።
4ከብዙ ውኆች ድምፅ የተነሣ
የባሕር እንቅስቃሴዋ#ዕብ. “ሞገድ” ይላል። ድንቅ ነው።
ድንቅስ በልዕልና የሚኖር እግዚአብሔር ነው።
5ምስክርህ እጅግ የታመነ ነው፤
አቤቱ፥ እስከ ረዥም ዘመን ድረስ ለቤትህ ምስጋና#ዕብ. “ቅድስና” ይላል። ይገባል።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 92: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fam.png&w=128&q=75)
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ