መዝሙረ ዳዊት 95
95
ከምርኮ በኋላ ቤት በተሠራ ጊዜ።
1ለእግዚአብሔር አዲስ ምስጋናን አመስግኑ፤
ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑት።
2እግዚአብሔርንም አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፥
ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።
3ክብሩን ለአሕዛብ፥
ተአምራቱንም ለወገኖች ሁሉ ንገሩ፤
4እግዚአብሔር ታላቅ፥ ምስጋናውም ብዙ ነውና፥
በአማልክትም ሁሉ ላይ የተፈራ ነውና።
5የአሕዛብ አማልክት ሁሉ አጋንንት ናቸውና፤
እግዝአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ።
6እምነትና በጎነት በፊቱ፥
ቅድስናና የክብር ገናናነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።
7የአሕዛብ ወገኖች፥ ለእግዚአብሔር አምጡ፥
ክብርንና ምስጋናን ለእግዚአብሔር አምጡ፤
8ለእግዚአብሔር ለስሙ ክብርን አምጡ፤
መሥዋዕት ያዙ ወደ አደባባዮችም ግቡ።
9ለእግዚአብሔር በቅድስናው ቦታ ስገዱ፤
ምድር በመላዋ ከእግዚአብሔር ፊት የተነሣ ትነዋወጣለች።
10እግዚአብሔር አንደ ነገሠ ለአሕዛብ ንገሩአቸው፥
እንዳይናወጥም ዓለሙን ሁሉ አጸናው፥
አሕዛብንም በቅንነት ይገዛል።
11ሰማያት ደስ ይላቸዋል፥ ምድርም ሐሤትን ታደርጋለች፤
ባሕር ሞላዋ ትናወጣለች፤
12በረሃ በእርስዋም ያሉ ሁሉ ሐሤትን ያደርጋሉ፤
የዱር ዛፎች ሁሉ በዚያን ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ደስ ይላቸዋል፤
13ይመጣልና፤ በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣልና፤
እርሱም ዓለምን በጽድቅ አሕዛብንም በቅንነት ይገዛል።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 95: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ