መጽ​ሐፈ ተግ​ሣጽ 1

1
1 # ምዕ. 1 በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ እና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ምሳሌ ምዕ. 25 ነው። የይ​ሁዳ ንጉሥ የሕ​ዝ​ቅ​ያስ ወዳ​ጆች ያለ ጥር​ጥር የጻ​ፉት የተ​ለ​ያየ የሰ​ሎ​ሞን ተግ​ሣጽ ነው።
2የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብር ነገ​ርን ይሰ​ው​ራል፥
የን​ጉሥ ክብር ግን ነገ​ርን ያከ​ብ​ራል።
3ሰማይ ከፍ ያለ ነው፥ ምድ​ርም ጥልቅ ነው፥
የን​ጉሥ ልብም እን​ዲሁ አይ​ታ​ወ​ቅም።
4ያል​ጠ​ራ​ውን ብር አጥ​ራው፥
ፈጽ​ሞም ይጠ​ራል።
5ከን​ጉሡ ፊት ክፉ​ዎ​ችን አጥፋ፥
ዙፋ​ኑም በጽ​ድቅ ይቀ​ናል።
6በን​ጉሥ ፊት አት​ታ​በይ፥
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት አት​መ​ጻ​ደቅ፥#“በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት አት​መ​ጻ​ደቅ” የሚ​ለው በዕብ. እና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም።
በመ​ኳ​ን​ንት ስፍራ አት​ቁም፤
7በመ​ኰ​ንን ፊት ከም​ቷ​ረድ፦
ወደ​ዚህ ከፍ በል ብት​ባል ይሻ​ል​ሃ​ልና፥
ዐይ​ኖ​ችህ ያዩ​ትን ተና​ገር።
8ኋላ እን​ዳ​ት​ጸ​ጸት፥
ለጥል ፈጥ​ነህ አት​ውጣ።
ክር​ክ​ርን ከባ​ል​ን​ጀ​ራህ ጋር ተከ​ራ​ከር፥
ምሥ​ጢ​ሩ​ንም አት​ግ​ለጥ።
9ባል​ን​ጀ​ራህ በነ​ቀ​ፈህ ጊዜ ወደ​ኋ​ላህ ተመ​ለስ፥
ባል​ን​ጀ​ራ​ህም እን​ዳ​ይ​ነ​ቅ​ፍህ ቸል አት​በ​ለው፥
ጠብ​ህም ክር​ክ​ር​ህም ከእ​ርሱ አያ​ር​ቅ​ህም።
10ምሥ​ጢ​ሩን ብት​ገ​ልጥ ግን የሞት ያህል ይሆ​ን​ብ​ሃል፥
ጸጋና ወን​ድ​ማ​ማ​ች​ነ​ትም ነጻ ያደ​ር​ጋል።
ነገር ግን መዘ​ባ​በቻ እን​ዳ​ት​ሆን ራስ​ህን ጠብቅ፤
በመ​ል​ካም ሥራ​ህም መን​ገ​ዶ​ች​ህን ጠብቅ።
11በብር ጻሕል ላይ ያለ የወ​ርቅ ዕን​ኰይ ያማረ እን​ደ​ሚ​ሆን፥
በየ​መ​ልኩ የሚ​ና​ገ​ሩት ቃልም እን​ዲሁ ነው።
12በወ​ርቅ ጉትቻ ላይ ያለ ዋጋው ብዙ የሆነ ሰር​ድ​ዮን የሚ​ባል የዕ​ንቍ ፈርጥ ያማረ እን​ደ​ሆነ፥
እን​ደ​ዚሁ የብ​ልህ ነገር በሚ​ሰማ ሰው ጆሮ ያማረ ነው።
13በመ​ከር ወራት በቈላ የው​ርጭ ጠል ደስ እን​ደ​ሚ​ያ​ሰኝ፥
እን​ዲሁ የታ​መነ መል​እ​ክ​ተኛ ለላ​ኩት ይጠ​ቅ​ማል።
የጌ​ቶ​ቹን ነፍስ ያሳ​ር​ፋ​ልና።
14በሐ​ሰ​ተኛ ሀብት የሚ​መኩ ሁሉ፥
ዝናብ እን​ደ​ሌ​ላ​ቸው ደመ​ና​ትና ነፋ​ሳት ናቸው።
15የሕ​ይ​ወት ውበት በት​ዕ​ግ​ሥት ትነ​ግ​ሣ​ለች፥#ዕብ. “በት​ዕ​ግ​ሥት አለቃ ይለ​ዝ​ባል” ይላል።
ልዝብ አን​ደ​በ​ትም አጥ​ን​ትን ትሰ​ብ​ራ​ለች።
16ልጄ ሆይ፥ አጥ​ብ​ቀህ እን​ዳ​ት​ጠ​ግብ፥ እን​ዳ​ት​ተ​ፋ​ውም
ማር ባገ​ኘህ ጊዜ በልኩ ብላ።
17እን​ዳ​ይ​ሰ​ለ​ችህ እን​ዳ​ይ​ጠ​ላ​ህም፥
እግ​ር​ህን ወደ ባል​ጀ​ራህ ቤት አታ​ዘ​ው​ትር።
18በባ​ል​ጀ​ራው ላይ በሐ​ሰት የሚ​መ​ሰ​ክር፥
እንደ በት​ርና እንደ ሰይፍ እንደ ተሳ​ለም ፍላጻ ነው።
19የክፉ መን​ገ​ድና የኀ​ጢ​አ​ተኛ እግር፥
በክፉ ቀን ይጠ​ፋሉ።
20መጻጻ ለቍ​ስል እን​ደ​ማ​ይ​መች፥
እን​ደ​ዚ​ሁም በሥጋ ላይ የሚ​ወ​ርድ ነውር ልብን ያሳ​ዝ​ናል።
ነቀዝ ዕን​ጨ​ትን፥ ብልም ልብ​ስን እን​ደ​ሚ​በ​ላው፥
እን​ደ​ዚሁ ኀዘን የሰ​ውን ልብ ትጐ​ዳ​ለች።
21ጠላ​ትህ ቢራብ አብ​ላው፥
ቢጠ​ማም አጠ​ጣው።
22ይህን ብታ​ደ​ርግ በራሱ ላይ ፍም ትሰ​በ​ስ​ባ​ለህ፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መል​ካም ዋጋ​ህን ይመ​ል​ስ​ል​ሃል።
23የሰ​ሜን ነፋስ ወጀብ ያመ​ጣል፤
ፊትን የማ​ያ​ፍር ምላ​ስም ያስ​ቈ​ጣል።
24ከነ​ዝ​ናዛ ሴት ጋር ባማረ ቤት ከመ​ቀ​መጥ፥
አንድ ጎኑ በፈ​ረሰ ግንብ መቀ​መጥ ይሻ​ላል።
25የቀ​ዘ​ቀዘ ውኃ ለተ​ጠ​ማች ሰው​ነት መል​ካም እንደ ሆነ፥
ከሩቅ ሀገር የመጣ የም​ሥ​ራ​ችም እን​ዲሁ መል​ካም ነው።
26በኃ​ጥ​ኣን ፊት የጻ​ድቅ መው​ደቅ፥
ጕድ​ጓ​ድን እንደ መዝ​ጋ​ትና የውኃ መው​ጫን እንደ ማጥ​ፋት ነው።
27ብዙ ማር መብ​ላት መል​ካም አይ​ደ​ለም፤
እን​ዲ​ሁም የራ​ስን ክብር መፈ​ለግ አያ​ስ​ከ​ብ​ርም።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የከ​በ​ረ​ውን ቃል ማክ​በር ይገ​ባል” ይላል።
28ቅጥር እን​ደ​ሌ​ላት እንደ ፈረ​ሰች ከተማ፥
ያለ ምክር የሚ​ኖር ሰው እን​ዲሁ ነው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ