መጽ​ሐፈ ሲራክ 44

44
የቀ​ደሙ አባ​ቶች ውዳሴ
1የከ​በሩ ሰዎ​ች​ንና አባ​ቶ​ቻ​ች​ንን በዘ​መ​ና​ቸው እና​መ​ስ​ግ​ና​ቸው።
2እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብዙ ክብ​ርን ሰጥ​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥
ከመ​ጀ​መ​ሪያ ጀምሮ አግ​ን​ኖ​አ​ቸ​ዋ​ልና።
3በኀ​ይ​ላ​ቸው ስማ​ቸ​ውን ያስ​ጠሩ፥ በጥ​በ​ባ​ቸው የሚ​መ​ክሩ፥
ትን​ቢ​ት​ንም የሚ​ና​ገሩ ሰዎች በመ​ን​ግ​ሥ​ታ​ቸው ገዙ።
4የአ​ሕ​ዛብ ነገ​ሥ​ታት በሰ​ል​ፋ​ቸው፥
የሕ​ዝ​ቡም ጸሓ​ፊ​ዎች በም​ክ​ራ​ቸው፥ በል​ባ​ቸ​ውም ባለ በቃ​ላ​ቸው ጥበብ፤
5ምስ​ጋ​ና​ንና ያማረ መሰ​ን​ቆን የሚ​ፈ​ልጉ፥
በመ​ጽ​ሐፍ እንደ ተጻፈ አድ​ር​ገው የሚ​ያ​መ​ሰ​ግኑ፥
6ባለ​ጸ​ጎች የሆኑ ገን​ዘ​ባ​ቸው የሚ​በ​ቃ​ቸው፥
በቤ​ታ​ቸው በደ​ኅና የሚ​ኖሩ ሰዎ​ችም፤
7እነ​ዚህ ሁሉ በዘ​መ​ና​ቸው የከ​በሩ፥
በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸ​ውም የተ​ዘ​ጋጁ ናቸው፤
8ከእ​ነ​ር​ሱም ውዳ​ሴ​ያ​ቸው ይነ​ገር ዘንድ፥
የከ​በረ ስምን የተዉ አሉ።
9የሚ​ያ​ስ​ባ​ቸው የሌለ፥ የጠ​ፉም፥
እን​ዳ​ል​ተ​ፈ​ጠ​ሩና እን​ዳ​ል​ተ​ወ​ለዱ የሆ​ኑም አሉ።
ልጆ​ቻ​ቸ​ውም ከእ​ነ​ርሱ ጋራ እንደ እነ​ርሱ ጠፉ።
10እነ​ዚህ ግን ጽድ​ቃ​ቸው ያል​ተ​ዘ​ነ​ጋ​ች​ባ​ቸው፥
ይቅ​ር​ታን የተ​ሞሉ ናቸው፤
11ያማ​ረች ርስ​ታ​ቸ​ውም ከል​ጆ​ቻ​ቸው ጋራ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ጸንታ ትኖ​ራ​ለች።
ልጆ​ቻ​ቸ​ውም በሥ​ር​ዐ​ታ​ቸው ይኖ​ራሉ።
12ዘራ​ቸው ፈጥኖ ይቆ​ማል፥
ልጆ​ቻ​ቸ​ውም በእ​ነ​ርሱ ፋንታ ናቸው፤
13ዘራ​ቸ​ውም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል፤
ክብ​ራ​ቸ​ውም አያ​ል​ቅም።
14ሥጋ​ቸ​ውም በሰ​ላም ተቀ​በረ፤
ስማ​ቸ​ውም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ጸንታ ትኖ​ራ​ለች።
15አሕ​ዛ​ብም ጥበ​ባ​ቸ​ውን ይና​ገ​ራሉ፤
በአ​ሕ​ዛ​ብም ሸንጎ ያመ​ሰ​ግ​ኗ​ቸ​ዋል።
ስለ ሄኖ​ክና ኖኅ
16ሄኖክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ አሰ​ኘው፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እር​ሱን ሰወ​ረው፤
ንስ​ሓም ይገቡ ዘንድ ለት​ው​ልድ ሁሉ አብ​ነት ሆነ።
17ኖኅም ፍጹ​ምና ጻድቅ ሆኖ ተገኘ፤
በጥ​ፋ​ትም ዘመን እርሱ ለዓ​ለም ምክ​ን​ያት ሆነ፤
የጥ​ፋ​ትም ውኃ በወ​ረደ ጊዜ እርሱ ለም​ድር ዘር ሆኖ ቀረ።
18የጥ​ፋት ውኃ ሰውን ሁሉ እን​ዳ​ያ​ጠ​ፋው፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ርሱ ጋር ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ቃል ኪዳን አደ​ረገ።
ስለ አብ​ር​ሃም
19የአ​ሕ​ዛብ ሁሉ አባት አብ​ር​ሃም ታላቅ ነው፤
የል​ዑ​ልን ሕግ የጠ​በቀ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ቃል ኪዳን ያደ​ረገ፥
በክ​ብር እር​ሱን የሚ​መ​ስል አል​ተ​ገ​ኘም።
20እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሰ​ው​ነቱ ቃል ኪዳ​ንን አጸ​ና​ለት።
በፈ​ተ​ነ​ውም ጊዜ የታ​መነ ሆኖ ተገኘ።
21ስለ​ዚ​ህም አሕ​ዛብ በዘሩ ይባ​ረኩ ዘንድ፥
እንደ ባሕር አሸ​ዋም ያበ​ዛ​ቸው ዘንድ፥
ዘሩም እንደ ሰማይ ከዋ​ክ​ብት ይበዙ ዘንድ፥
ከባ​ሕር እስከ ባሕ​ርም ድረስ ያወ​ር​ሳ​ቸው ዘንድ፥
ከወ​ን​ዞ​ችም እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ያወ​ር​ሳ​ቸው ዘንድ ቃል ኪዳ​ንን አጸ​ና​ለት፥
ይስ​ሐ​ቅና ያዕ​ቆብ
22ለይ​ስ​ሐ​ቅም ስለ አባቱ ስለ አብ​ር​ሃም ደግ​ነት፥
ለሰው ሁሉ የም​ት​ሆን በረ​ከ​ት​ንና ቃል ኪዳ​ንን አጸ​ና​ለት።
23በያ​ዕ​ቆብ ራስ ላይም ዐረ​ፈች፥
በረ​ከ​ቱም ተገ​ለ​ጠ​ች​ለት፥
እር​ሷ​ንም ርስት አድ​ርጎ ሰጠው፤ ርስ​ታ​ቸ​ው​ንም በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ለየ​ላ​ቸው፥
ለዐ​ሥራ ሁለቱ ነገ​ድም ርስ​ታ​ቸ​ውን ከፈ​ለ​ላ​ቸው።
24ከእ​ነ​ር​ሱም የከ​በ​ሩና በሰው ዘንድ ሞገ​ስን ያገኙ፥
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በሰው ዘን​ድም የተ​ወ​ደዱ ጻድ​ቃን ሰዎ​ችን አስ​ነሣ።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከእ​ርሱ የከ​በ​ረና በሰው ዘንድ ሞገ​ስን ያገኘ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በሰው ዘንድ የተ​ወ​ደደ ሰውን አስ​ነሣ” ይላል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ