መጽ​ሐፈ ሲራክ 45

45
ሙሴ
1ሙሴም ስም አጠ​ራሩ የተ​ባ​ረከ ነው፤
መታ​ሰ​ቢ​ያ​ውና አም​ሳ​ሉም እንደ ቅዱ​ሳን ክብር ነው።
2ከፍ ከፍም አደ​ረ​ገው፤
በጠ​ላ​ቶ​ቹም ላይ የሚ​ያ​ስ​ፈራ ሆነ።
3በቃ​ሉም ተአ​ም​ራ​ትን አደ​ረገ፤
በነ​ገ​ሥ​ታ​ቱም ፊት አከ​በ​ረው፤
ስለ ሕዝ​ቡም አዘ​ዘው፤ ክብ​ሩ​ንም አሳ​የው።
4ስለ ሃይ​ማ​ኖ​ቱና ስለ የዋ​ህ​ነ​ቱም ቀደ​ሰው፤
ከሰ​ውም ሁሉ እር​ሱን መረ​ጠው።
5ቃሉ​ንም አሰ​ማው፤
ወደ ደመ​ና​ውም ውስጥ አገ​ባው፤
ትእ​ዛ​ዙ​ንም በፊቱ ሰጠው፤
ለያ​ዕ​ቆብ ቃል ኪዳ​ኑን፥ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ፍር​ዱን ያስ​ተ​ምር ዘንድ የሕ​ይ​ወት ሕግን ሰጠው።
አሮን
6ከሌዊ ወገን የተ​ወ​ለደ ወን​ድሙ አሮ​ንም እንደ እርሱ ታላቅ ነው፤
ቅዱ​ስም፥ የከ​በ​ረም ነው።
7የዘ​ለ​ዓ​ለም ሕግ​ንም አጸ​ና​ለት፤
በሕ​ዝ​ቡም መካ​ከል ክህ​ነ​ትን ሰጠው፤
በአ​ማረ ጌጥም አስ​ደ​ነ​ቀው፤
የክ​ብር ልብ​ስ​ንም አለ​በ​ሰው።
8በሁ​ሉም ዘንድ አስ​መ​ካው፤
በከ​በሩ ልብ​ሶ​ችም አጸ​ናው፤
እጀ ሰፊና እጀ ጠባ​ብ​ንም፥ ኤፉ​ድ​ንም አለ​በ​ሰው።
9በዙ​ሪ​ያ​ውም ብዙ ሮማ​ንና የወ​ርቅ ጸና​ጽል አለ፤
በእ​ግ​ሩም በረ​ገጠ ጊዜ የመ​ር​ገፉ ድምፅ በቤተ መቅ​ደስ ይሰማ ዘንድ ይጮህ ነበር፤
ይህም ለሕ​ዝ​ቡና ለል​ጆ​ቻ​ቸው መታ​ሰ​ቢያ ሆነ።
10የተ​ለየ ሰማ​ያዊ ሐር ያለ​በት አራት ኅብ​ርን፥
አም​ስ​ተኛ ወርቀ ዘቦ ያለ​በት በነጭ ሐር የተ​ሠራ ልብ​ስ​ንም፥
በሚ​ገ​ባና በእ​ው​ነት ነገር የተ​ሠራ ልብሰ መት​ከፍ አለ​በ​ሰው።
11የነጭ ሐር የሚ​ሆን ፈትሉ እጥፍ የሆነ፥
ዕን​ቍም ያለ​በት፥
የማ​ኅ​ተ​ምም ቅርጽ ያለ​በት ልብ​ስን በል​ብስ ላይ አለ​በ​ሰው፤
እጀ ጠባ​ቡም በወ​ርቅ የተ​ሠራ ነው፤
በየ​ወ​ገ​ና​ቸው መታ​ሰ​ቢያ ሊሆን በዐ​ሥራ ሁለቱ ነገደ እስ​ራ​ኤል ልጆች ቍጥር ልክ የተ​ጻፈ ነው።
12በማ​ኅ​ተም መልክ አም​ሳል የተ​ሠራ የወ​ርቅ አክ​ሊ​ልን
በዝ​ግራ መጠ​ም​ጠ​ሚ​ያው ላይ አደ​ረ​ገ​ለት፤
የተ​ለየ የክ​ብሩ መመ​ኪያ የሚ​ሆን ተአ​ም​ራት የሚ​ያ​ደ​ር​ግ​በት፥
ለዐ​ይን የተ​ወ​ደደ፥ ጌጡ ፈጽሞ ያማረ የወ​ርቅ መጠ​ም​ጠ​ሚ​ያን በዝ​ግራ መጠ​ም​ጠ​ሚ​ያው ላይ አደ​ረ​ገ​ለት።
13ከእ​ርሱ አስ​ቀ​ድሞ እንደ እርሱ ልብስ ያለ ልብስ አል​ተ​ሠ​ራም፤
ከል​ጆቹ ብቻ በቀር፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ከዘ​መ​ዶ​ቹም በቀር እንደ እርሱ የለ​በሰ የለም።
14ሁል​ጊዜ በየ​ዕ​ለቱ የጧ​ትና የማታ መሥ​ዋ​ዕት ይሠ​ዉ​ለት ዘንድ፥
15ሙሴም እጃ​ቸ​ውን ቀባ​ላ​ቸው፤
የተ​ቀ​ደ​ሰ​ው​ንም ዘይት ቀባው፤
ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም ሕግ ሆነው፤ ይገ​ዙ​ለት ዘንድ፤ ካህ​ና​ትም ይሆ​ኑት ዘንድ፤ ሕዝ​ቡ​ንም በስሙ ይባ​ር​ኳ​ቸው ዘንድ፤
ሰማይ ጸንቶ በሚ​ኖ​ር​በት ዘመን ልክ ለል​ጆቹ ሕግ ሆና​ቸው።
16ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሥ​ዋ​ዕት ይሠዋ ዘንድ፥
የበጎ መዓዛ መታ​ሰ​ቢ​ያም ሊሆን ዕጣ​ንን ያጥን ዘንድ፥
ለሕ​ዝ​ቡም ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ያስ​ተ​ሰ​ር​ይ​ላ​ቸው ዘንድ ከሕ​ያ​ዋን ሁሉ እር​ሱን መረጠ።
17ትእ​ዛ​ዛ​ቱን ሰጠው፤
ለያ​ዕ​ቆብ ምስ​ክ​ሩን ያስ​ተ​ም​ረው፥
ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሕጉን ያስ​ተ​ም​ረው ዘንድ ፍር​ድ​ንና ሥል​ጣ​ንን ሰጠው።
18ሌሎች ግን ተቃ​ወ​ሙት፤
የዳ​ታ​ንና የአ​ቤ​ሮን የሆኑ ሰዎች፥ የእ​ነ​ቆ​ሬም ሠራ​ዊት
በመ​ና​ደ​ድና በመ​ቈ​ጣት በም​ድረ በዳ ቀኑ​በት።
19እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አያ​ቸው፤ ደስም አላ​ሰ​ኙ​ትም፤
ተቈ​ጥ​ቶም አጠ​ፋ​ቸው፤
በእ​ነ​ር​ሱም ላይ ድንቅ ተአ​ም​ራ​ትን አደ​ረገ፤
በእ​ሳ​ትም አጠ​ፋ​ቸው።
20ለአ​ሮ​ንም ክብ​ርን ጨመ​ረ​ለት፤
የእ​ህ​ላ​ቸ​ው​ንም ቀዳ​ም​ያት ዕድል ፋንታ አድ​ርጎ ሰጠው።
21ለእ​ር​ሱና ለል​ጆ​ቹም የሰ​ጣ​ቸ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መሥ​ዋ​ዕት ይበሉ ዘንድ፥
የሚ​ያ​ጠ​ግ​ባ​ቸው ዐሥ​ራ​ቱን አስ​ቀ​ድሞ ሠራ​ላ​ቸው።
22የሕ​ዝ​ቡ​ንም ምድር አል​ተ​ካ​ፈ​ለም፤
ከሕ​ዝ​ቡም ጋራ ርስ​ትን አል​ወ​ረ​ሰም፤
እርሱ ራሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዕድሉ፥ ርስ​ቱም ነውና።
ፊን​ሐስ
23የአ​ል​ዓ​ዛር ልጅ ፊን​ሐ​ስም በክ​ብር ሦስ​ተኛ ነው፤
ለአ​ም​ል​ኮተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀን​ቶ​አ​ልና፥
ሕዝ​ቡ​ንም ለማ​ስ​ተ​ማር አስ​ነ​ሥ​ቶ​ታ​ልና፥
በል​ቡ​ናው ቸር​ነ​ትም ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈቃድ የተ​ነሣ ለእ​ስ​ራ​ኤል አስ​ተ​ሰ​ረየ።
24ስለ​ዚ​ህም ለሕ​ዝቡ የቅ​ዱ​ሳ​ንን ሥር​ዐት ያስ​ተ​ም​ራ​ቸው ዘንድ፥
ለእ​ር​ሱና ለዘ​ሩም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ደገኛ ክህ​ነት ይሆን ዘንድ የሰ​ላም ኪዳ​ንን አጸ​ና​ለት።
25ከነ​ገደ ይሁዳ ለተ​ወ​ለደ ለዳ​ዊት ልጅም ጌጥ ይሆን ዘንድ፥
በሕጉ ጸንቶ የሚ​ኖር የልጁ መን​ግ​ሥ​ትም እድል ይሆን ዘንድ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የመ​ን​ግ​ሥት ርስት ለዘሩ ብቻ ይሆን ዘንድ ከይ​ሁዳ ወገን ለሆ​ነው ለዕ​ሴይ ልጅ ለዳ​ዊት እን​ዳ​ደ​ረ​ገው ቃል ኪዳን እን​ዲሁ የአ​ሮን ርስት ለዘሩ ይሆን ዘንድ” ይላል።
26በል​ቡ​ና​ቸ​ውም ጥበ​ብን ያሳ​ድ​ር​ባ​ቸው ዘንድ፥
በዘ​መ​ና​ቸው ሁሉ ክብ​ራ​ቸ​ውና በረ​ከ​ታ​ቸው እን​ዳ​ይ​ጠ​ፋ​ባ​ቸው፥
ወገ​ኖ​ቹ​ንም በእ​ው​ነት ይገ​ዟ​ቸው ዘንድ ከል​ጆቹ ጋራ ለእ​ርሱ ክህ​ነት ርስቱ ነው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ