መጽ​ሐፈ ሲራክ 46

46
ኢያ​ሱና ካሌብ
1የነዌ ልጅ ኢያ​ሱም በሰ​ልፍ ውስጥ ጽኑዕ ነው። ከሙ​ሴም ቀጥሎ ትን​ቢት ተና​ገረ፤
እንደ ስሙም ታላቅ ሆነ፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የመ​ረ​ጣ​ቸ​ው​ንም ከመ​ከራ አዳ​ና​ቸው፤
ለእ​ስ​ራ​ኤል ምድ​ራ​ቸ​ውን ያወ​ር​ሳ​ቸው ዘንድ ጠላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ተበ​ቅሎ አጠፋ።
2እጁን በአ​ነሣ ጊዜ፥
በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ላይ ጦሩን በወ​ረ​ወረ ጊዜ ከበረ።
3ከእ​ርሱ አስ​ቀ​ድሞ እንደ እርሱ የሆነ ማን​ነው?
እርሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ጠላ​ቶ​ቹን ተዋ​ጋ​ለት።
4ፀሐይ በቃሉ የቆ​መች አይ​ደ​ለ​ምን?
አን​ዲ​ቱስ ቀን ሁለት ቀን የሆ​ነች አይ​ደ​ለ​ምን?
5በዙ​ሪ​ያው ያሉ ጠላ​ቶቹ በአ​ስ​ጨ​ነ​ቁት ጊዜ
ኀያ​ልና ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ጠራው፤
ገናና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በበ​ረ​ድና በጽ​ኑዕ ኀይል መለ​ሰ​ለት።
6በተ​ጣ​ሏ​ቸው በአ​ሕ​ዛ​ብም ላይ አዘ​ነ​በ​ባ​ቸው፤
የተ​ዋ​ጓ​ቸ​ው​ንም በገ​ደል ውስጥ አጠ​ፏ​ቸው፤
ሕዝቡ ኀይ​ሉን ያውቁ ዘንድ የሚ​ዋ​ጋ​ላ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነውና፤
ኀይ​ሉን አከ​ታ​ትሎ ከእ​ነ​ርሱ ጋር አደ​ረ​ገ​ላ​ቸው።
7በሙ​ሴም ዘመን ከእ​ነ​ርሱ ጋር ይቅ​ር​ታን አደ​ረገ፤
እር​ሱና የዮ​ፎኒ ልጅ ካሌብ በጠ​ላት ፊት ተከ​ራ​ከሩ፤
ሕዝ​ቡ​ንም በደ​ልን ከለ​ከ​ሏ​ቸው፥
ክፉ እን​ጕ​ር​ጕ​ሮ​ንም አስ​ተ​ዉ​አ​ቸው።
8ከስ​ድ​ስት መቶ ሺህ አር​በ​ኞ​ችም የዳኑ እነ​ርሱ ሁለቱ ብቻ ናቸው፤
ወተ​ትና ማር ወደ​ም​ታ​ፈ​ስስ ወደ ከነ​ዓ​ንም ገቡ።
9እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለካ​ሌብ ኀይ​ልን ሰጠው፤
እስ​ኪ​ያ​ረ​ጅም ድረስ ከእ​ርሱ ጋራ ኖረ፤
ወደ ከፍ​ተ​ኛ​ውም ምድር አወ​ጣው።
ልጆ​ቹም ርስ​ታ​ቸ​ውን ተካ​ፈሉ።
10የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መከ​ተል መል​ካም እንደ ሆነ ያውቁ ዘንድ።
መሳ​ፍ​ንት
11በየ​ስ​ማ​ቸው የተ​ጠሩ የእ​ስ​ራ​ኤል መሳ​ፍ​ንት፥
ልቡ​ና​ቸ​ውም ያል​ሰ​ሰነ ሰዎች ሁሉ፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ያል​ተ​ዉት ሰዎች ሁሉ፥
ስም አጠ​ራ​ራ​ቸው የተ​ባ​ረከ ይሁን።
12በኖ​ሩ​በ​ትም ሀገር አጥ​ን​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ደስ ይበ​ላ​ቸው፤
ልጆ​ቻ​ቸ​ውም ይባ​ረኩ፥ ይክ​በሩ።#ግሪኩ “የተ​ባ​ረከ ስማ​ቸ​ውም በል​ጆ​ቻ​ቸው ይኑር” ይላል።
13ሳሙ​ኤ​ልም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የተ​ወ​ደደ ነበር፤
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ዘንድ ነቢይ ነበር፤
ለሕ​ዝቡ ንጉ​ሥን ቀብቶ አነ​ገሠ።
14በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕግ ማኅ​በ​ሩን ገዛ፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ያዕ​ቆ​ብን አከ​በ​ረው።
15በእ​ም​ነ​ቱም ትን​ቢት ጸና፤
በቃ​ሉም እው​ነ​ተኛ ራእይ ተገ​ለጠ።
16የበ​ግም ጠቦት ሲሠዋ ጠላ​ቶቹ ከብ​በው በአ​ስ​ጨ​ነ​ቁት ጊዜ
ኀያል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ጠራው።
17እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሰ​ማይ አን​ጐ​ደ​ጐደ፤
በታ​ላቅ ጩኸ​ትም ድም​ፁን አሰማ።
18የፍ​ል​ስ​ጥ​ኤ​ም​ንና የጤ​ሮ​ስ​ንም ነገ​ሥ​ታት ሁሉ አጠ​ፋ​ቸው።
19የሚ​ሞ​ት​በ​ትም ቀን ሳይ​ደ​ርስ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና ለመ​ሢሑ፥
የማ​ን​ንም ሰው ገን​ዘብ ከገ​ን​ዘ​ባ​ቸው እስከ ጫማ ድረስ እን​ዳ​ል​ወ​ሰደ፥
ከእ​ነ​ር​ሱም የከ​ሰ​ሰው እን​ደ​ሌለ አዳኘ።
20ከሞ​ተም በኋላ ትን​ቢት ተና​ገረ፤
የን​ጉ​ሡ​ንም ሞት ተና​ገረ፤
ከም​ድ​ርም ተነ​ሥቶ ቃሉን በት​ን​ቢት ከፍ አደ​ረገ።
የሕ​ዝ​ቡ​ንም በደል አጠፋ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ