መጽ​ሐፈ ሲራክ 47

47
ናታ​ንና ዳዊት
1ከእ​ር​ሱም በኋላ ናታን ተነሣ፤
በዳ​ዊ​ትም ዘመን ትን​ቢት ተና​ገረ።
2ስቡን ከድ​ኅ​ነቱ መሥ​ዋ​ዕት እን​ደ​ሚ​ለዩ
እን​ደ​ዚሁ ዳዊት ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ተለየ።
3በእ​ር​ሱም ዘንድ አን​በሳ እንደ ፍየል ጠቦት፥
ግስ​ላም እንደ በግ ጠቦት ነበር።
4በወ​ጣ​ት​ነቱ አር​በ​ኛን የገ​ደለ አይ​ደ​ለ​ምን?
እጁ​ንስ አን​ሥቶ ድን​ጋይ በወ​ነ​ጨፈ ጊዜ ጎል​ያ​ድን ግን​ባ​ሩን የመ​ታው፥ ናላ​ው​ንም የበ​ጠ​በ​ጠው አይ​ደ​ለ​ምን?
የሕ​ዝ​ቡ​ንስ ተግ​ዳ​ሮት ያስ​ወ​ገደ አይ​ደ​ለ​ምን?
5ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ለም​ኖ​ታ​ልና
በሰ​ልፍ ኀይ​ለ​ኛ​ውን ሰው ይገ​ድል ዘንድ
የወ​ገ​ኖ​ቹ​ንም ቀንድ ያጸና ዘንድ በቀኝ እጁ ኀይ​ልን ሰጠው።
6ዘፋ​ኞ​ቹም ዳዊ​ትን ዐሥር ሺህ ገዳይ አሉት፤
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በረ​ከት አመ​ሰ​ገ​ኑት፤
የክ​ብር ዘው​ድ​ንም ተቀ​ዳጀ።
7በዙ​ሪ​ያው ያሉ ጠላ​ቶ​ቹ​ንም ቀጠ​ቀ​ጣ​ቸው፤
ጠላ​ቶቹ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ን​ንም አዋ​ረ​ዳ​ቸው፤
እስከ ዛሬም ድረስ ቀን​ዳ​ቸ​ውን#“ኀይ​ላ​ቸ​ውን ደመ​ሰሰ” ማለት ነው። ሰበረ።
8በሚ​ሠ​ራው ሥራ ሁሉ ቅዱ​ስና ልዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በም​ስ​ጋና ቃል አመ​ሰ​ገነ፤
በፍ​ጹም ልቡም ፈጣ​ሪ​ውን አመ​ሰ​ገ​ነው፤ ወደ​ደ​ውም።
9በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ፊት መዘ​ም​ራ​ንን መደበ፤
የቃ​ላ​ቸ​ውም ዜማ ያማ​ረና የጣ​ፈጠ ነበር።
10መል​ካም በዓ​ል​ንም አደ​ረገ፤
ዓመ​ቱን ሁሉ ደስ አሰኘ፥
ቅዱስ ስሙ​ንም አመ​ሰ​ገ​ነው፤
ቅድ​ስ​ና​ውም ከነ​ግህ ጀምሮ ይነ​ገ​ራል።#ምዕ. 47 ቍ. 10 በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. “ዜማ​ውም በቤተ መቅ​ደሱ ከነ​ግህ ጀምሮ ያስ​ተ​ጋባ ነበር” ይላል።
11እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኀጢ​አ​ቱን አስ​ተ​ሰ​ረ​የ​ለት፤
ቀን​ዱ​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ከፍ ከፍ አደ​ረ​ገ​ለት፤
የተ​ባ​ረ​ከች መን​ግ​ሥ​ትን፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም የክ​ብር ዙፋን ሰጠው።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የን​ጉ​ሥ​ነ​ትን ቃል ኪዳን ሰጠው” ይላል።
ስለ ንጉሥ ሰሎ​ሞን
12ከእ​ር​ሱም በኋላ ጠቢብ የሆነ ልጁ ተተ​ካ​ለት
ስለ እር​ሱም በስ​ፋት ኖረ።
13ሰሎ​ሞ​ንም በሰ​ላም ዘመን ነገሠ፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዙ​ሪ​ያው ካሉት ሁሉ አሳ​ረ​ፈው፤
በስሙ ቤትን ሠራ፤ የዘ​ለ​ዓ​ለም መቅ​ደ​ሱ​ንም አዘ​ጋጀ።
14ሰሎ​ሞን ሆይ፥ ከሕ​ፃ​ን​ነ​ትህ ጀምሮ ጥበ​ብህ እን​ዴት በዛ፤
ማስ​ተ​ዋ​ል​ህም እንደ ፈሳሽ ውኃ ሞላ።
15ጥበ​ብህ ምድ​ርን ሸፈ​ነ​ቻት፥
ምሳ​ሌ​ህን፥ የነ​ገ​ር​ህ​ንም ትር​ጓሜ አበ​ዛህ።
16ስም​ህም እስከ ሩቅ ደሴት ድረስ ተሰማ፤
ስለ ሰላ​ም​ህም ተወ​ደ​ድህ።
17ሀገ​ሮ​ችም ስለ መዝ​ሙ​ርህ፥ ስለ ምሳ​ሌህ፥
ስለ እን​ቆ​ቅ​ል​ሾ​ች​ህና ስለ ትር​ጓ​ሜ​ዎ​ችህ አደ​ነ​ቁህ።
18የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በተ​ባለ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም፥
ወር​ቁ​ንም እንደ እር​ሳስ አደ​ለ​ብ​ኸው፤ ብር​ንም እንደ ማዕ​ድን ቅል​ቅል መላ​ኸው።
19ሴቶች ልቡ​ና​ህን ለወ​ጡት፤
በሥ​ጋ​ህም ሠለ​ጠ​ኑ​ብህ።
20ክብ​ር​ህን አስ​ነ​ቀ​ፍህ፤ ዘር​ህ​ንም አሳ​ደ​ፍኽ፤
በል​ጆ​ች​ህም ላይ መቅ​ሠ​ፍ​ት​ንና ጥፋ​ትን አመ​ጣህ፤
ስን​ፍ​ና​ህም አስ​ደ​ነ​ገ​ጠኝ።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በስ​ን​ፍ​ና​ህም አዘኑ” ይላል።
21መን​ግ​ሥ​ት​ህም ተከ​ፈለ፤
ዐመ​ፀኛ መን​ግ​ሥ​ትም ከኤ​ፍ​ሬም ወጣች።
22እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ቸር​ነ​ቱን አል​ተ​ወም፤
ሥራ​ው​ንም አላ​ጠ​ፋም፤ የጻ​ድ​ቃ​ኑ​ንም ልጆች አል​ደ​መ​ሰ​ሰም፤
የሚ​ወ​ዱ​ት​ንም ሰዎች ዘር አላ​ጠ​ፋም፤
ለያ​ዕ​ቆ​ብም ቅሬ​ትን ሰጠው፥ ከእ​ር​ሱም ለዳ​ዊት ሥርን ሰጠው።
ሮብ​አ​ምና ኢዮ​ር​ብ​አም
23ሰሎ​ሞ​ንም እንደ አባ​ቶቹ አረፈ
ከእ​ር​ሱም በኋላ አእ​ምሮ የሌ​ለው ልጁን ለእ​ስ​ራ​ኤል ተወ።
ይኸ​ውም ሕዝ​ቡን በም​ክሩ ያሳ​መ​ፃ​ቸው ሮብ​ዓም ነው።
እስ​ራ​ኤ​ልን ያሳ​ታ​ቸው፥ ለኤ​ፍ​ሬ​ምም የኀ​ጢ​አት መን​ገ​ድን ያሳየ የና​ባጥ ልጅ ኢዮ​ር​ብ​ዓም ነበረ።
24ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውም ፈጽሞ በዛ፥
ከሀ​ገ​ራ​ቸ​ውም አስ​ወ​ጥቶ ሰደ​ዳ​ቸው።
25ፍዳ​ቸ​ውም እስ​ክ​ት​ደ​ር​ስ​ባ​ቸው ድረስ ኀጢ​አ​ትን ሁሉ ፈለ​ጓት።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ