መጽ​ሐፈ ሲራክ 49

49
ንጉሡ ኢዮ​ስ​ያስ
1የኢ​ዮ​ስ​ያስ መታ​ሰ​ቢ​ያው በቀ​ማሚ ብል​ሃት እንደ ተቀ​መመ ሽቱ ነው፤
እንደ ማርም በአፍ ሁሉ ጣፋጭ ነው፤
በመ​ጠጥ ግብ​ዣም ጊዜ እንደ ዘፈን ነው።
2እርሱ የቀና ነው፤
ሕዝ​ቡ​ንም መለ​ሳ​ቸው፤
የኀ​ጢ​አ​ት​ንም ርኵ​ሰት ሁሉ አስ​ወ​ገደ።
3ልቡ​ና​ው​ንም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አቀና፤
በኃ​ጥ​ኣ​ንም ዘመን ጽድ​ቅን አጸ​ናት።
4ከዳ​ዊት፥ ከሕ​ዝ​ቅ​ያ​ስና ከኢ​ዮ​ስ​ያስ በቀር ሁሉም በድ​ለ​ዋል፤
የል​ዑ​ልን ሕግ ትተ​ዋ​ልና፤ የይ​ሁ​ዳም ነገ​ሥ​ታት አለቁ።
5ኀይ​ላ​ቸ​ውን ለሌላ ሰጥ​ተ​ዋ​ልና፥
ክብ​ራ​ቸ​ው​ንም ለሌላ ሕዝብ ሰጥ​ተ​ዋ​ልና።
ነቢዩ ኤር​ም​ያስ
6የተ​መ​ረ​ጠ​ች​ው​ንና የተ​ቀ​ደ​ሰ​ች​ውን ከተማ አቃ​ጠ​ሏት።
መከራ አጽ​ን​ተ​ው​ባ​ታ​ልና እንደ ነቢዩ ኤር​ም​ያስ ትን​ቢት ጎዳ​ና​ዋን አጠፉ።
7አሠ​ቃ​ይ​ተ​ው​ታ​ልና፤ እርሱ ግን ነቢይ ይሆን ዘንድ፥
ይነ​ቅል ዘንድ፥ ያጠ​ፋም ዘንድ፥
እን​ደ​ዚ​ሁም ይተ​ክል ዘንድ፥ ይሠ​ራም ዘንድ በእ​ናቱ ማኅ​ፀን ተመ​ረጠ።
ነቢዩ ሕዝ​ቅ​ኤል
8ሕዝ​ቅ​ኤ​ልም የጌ​ት​ነ​ቱን ራእይ አየ፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም በኪ​ሩ​ቤል ሠረ​ገላ ላይ አየው።
9ጠላ​ቶ​ቹ​ንም በመ​ዓት ዐሰ​ባ​ቸው፥
የጻ​ድ​ቃ​ን​ንም ጎዳ​ና​ቸ​ውን በመ​ል​ካም አቀና።
10የዐ​ሥራ ሁለቱ ነቢ​ያ​ትም አጽ​ሞ​ቻ​ቸው በየ​ቦ​ታ​ቸው ለመ​ለሙ፤
ያዕ​ቆ​ብን አጽ​ና​ን​ተ​ው​ታ​ልና፥ በታ​መነ ተስ​ፋም አድ​ነ​ው​ታ​ልና።
11ዘሩ​ባ​ቤ​ልን እን​ዴት እና​ገ​ን​ነው ይሆን!
እር​ሱስ በቀኝ እጅ እን​ዳለ እንደ ሐቲም ቀለ​በት ነው።
12የዮ​ሴ​ዴቅ ልጅ ዮሴ​ዕም እን​ዲሁ ነበረ፤
በዘ​መ​ና​ቸ​ውም ቤተ መቅ​ደ​ስን ሠሩ፤
ለዘ​ለ​ዓ​ለም ክብር የተ​ዘ​ጋጀ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሕዝብ አከ​በ​ሩት።
13የነ​ሕ​ም​ያም መታ​ሰ​ቢ​ያው ብዙ ነው፤
የወ​ደ​ቀ​ች​ውን ቅጽር አነ​ሣ​ልን፤
ደጃ​ፎ​ች​ንም አቆ​መ​ልን፤
ቍል​ፍ​ንም ሠራ​ልን፥ ቤታ​ች​ን​ንም ገነ​ባ​ልን።
14እንደ ሄኖክ ያለ ሰው በም​ድር የተ​ፈ​ጠረ የለም፤
እርሱ ከዚህ ዓለም ተወ​ሰደ።
15እንደ ዮሴ​ፍም ያለ ሰው አል​ተ​ወ​ለ​ደም፤
ለወ​ን​ድ​ሞቹ አለቃ ሆነ፤
ለሕ​ዝ​ቡም ኀይል ሆነ፥ ለአ​ጽ​ሞ​ቹም ይቅ​ር​ታን አገኘ።#ግሪኩ “አጥ​ን​ቶ​ቹም ክብ​ርን አገኙ” ይላል።
16ሴምና ሴት ከሰው ይልቅ ከበሩ፥
አዳ​ምም ከተ​ፈ​ጠ​ረው ሕያው ፍጥ​ረት ሁሉ ከበረ፤

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ