መጽ​ሐፈ ጥበብ 7

7
ሰው ሁሉ መዋቲ ስለ መሆኑ
1እኔም እንደ ሁሉ እኩል መዋቲ ሰው ነኝ፤ አስ​ቀ​ድሞ የተ​ፈ​ጠረ የም​ድ​ራዊ አዳም ልጅም ነኝ፥ በእ​ናቴ ማኅ​ፀ​ንም ሥጋ ሆኜ ተቀ​ር​ጫ​ለሁ። 2በመ​ገ​ና​ኘት ጊዜ ከአ​ባት ዘርና ከመ​ኝታ ፈቃድ ተገ​ኝቼ፥ ዐሥር ወር በደ​ም​ነት ረግቼ ኖርሁ። 3በተ​ፈ​ጠ​ር​ሁም ጊዜ እንደ ሰው ሁሉ ነፍ​ስን ነሣሁ፥ በመ​ከ​ራ​ዬም ምሳሌ ወደ ምድር ወረ​ድሁ፤ የቃ​ልም መጀ​መ​ርያ እንደ ሁሉ ልቅ​ሶን አለ​ቀ​ስሁ። 4በጨ​ርቅ ተጠ​ቅ​ልዬ በጥ​ን​ቃቄ አደ​ግሁ። 5ከነ​ገ​ሥ​ታት ወገን የል​ደቱ መጀ​መ​ሪያ ልዩ የሆነ የለ​ምና። 6የሁ​ሉም ወደ​ዚህ ዓለም አመ​ጣጡ አን​ዲት ናት፥ የሁ​ሉም መው​ጣቱ እኩል ነው።
ሰሎ​ሞን ለጥ​በብ የነ​በ​ረው ፍቅር
7ስለ​ዚህ ነገር ጸለ​ይሁ፤ ዕው​ቀ​ትም ተሰ​ጠኝ፤ ለመ​ንሁ፤ የጥ​በ​ብም መን​ፈስ ወደ እኔ መጣ። 8ከበ​ትረ መን​ግ​ሥ​ትና ከዙ​ፋ​ንም ይልቅ አከ​በ​ር​ኋት፤ ብዕ​ል​ንም ከእ​ር​ስዋ ጋር ሳመ​ዛ​ዝን እንደ ኢም​ንት አደ​ረ​ግ​ኋት። 9ወርቅ ሁሉ በእ​ርሷ ዘንድ እንደ ጥቂት አሸዋ ነውና፤ ብሩም በእ​ር​ስዋ ዘንድ እንደ ጭቃ ነውና፥ ዋጋ በሌ​ለው ዕንቍ አል​መ​ሰ​ል​ኋ​ትም። 10ከሕ​ይ​ወ​ትና ከው​በ​ትም ፈጽሜ ወደ​ድ​ኋት፤ ከእ​ርሷ የሚ​ወጣ የብ​ር​ሃን ነጸ​ብ​ራቅ አይ​ወ​ሰ​ን​ምና፥ ደግ​ሞም አይ​ጠ​ፋ​ምና ስለ ብር​ሃን ፋንታ ትሆ​ነኝ ዘንድ መረ​ጥ​ኋት።
11ከእ​ርሷ ጋር በአ​ን​ድ​ነት በጎ ነገር ሁሉ መጣ​ልኝ፤ ቍጥር የሌ​ለው ባለ​ጠ​ግ​ነ​ትም በእ​ጆ​ችዋ አለ። 12ጥበብ የእ​ነ​ዚህ ሁሉ አበ​ጋ​ዛ​ቸው ናትና በሁሉ ደስ አለኝ፤ ጥበብ የእ​ነ​ዚህ ሁሉ አስ​ገ​ኛ​ቸው እንደ ሆነች አላ​ወ​ቅ​ሁም ነበር። 13ይህን ባወ​ቅሁ ጊዜ ያለ ክፋ​ትና ያለ ቅን​አት እር​ሷን እሰ​ጣ​ለሁ፤ ብል​ጽ​ግ​ና​ዋ​ንም አል​ሰ​ው​ርም። 14ለሰ​ውም የማ​ያ​ልቅ መዝ​ገብ ናት፤ ገን​ዘብ ያደ​ረ​ጓ​ትም ሁሉ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ደረሱ፤ ሀብ​ትን የም​ት​ገ​ልጽ የም​ክር ሥራ ስለ ሆነ​ችም ተወ​ዳ​ጇት።
15ለእ​ኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ወ​ደ​ደ​ውን ነገር እና​ገር ዘንድ፥ ለሚ​ሰ​ጠ​ውም ሰው የሚ​ገ​ባ​ውን አስብ ዘንድ ጥበ​ብን ሰጠኝ። ወደ ጥበብ የሚ​መራ፥ ጠቢ​ባ​ን​ንም ቅን የሚ​ያ​ደ​ርግ እርሱ ነውና። 16እኛ ሁላ​ችን በእጁ ነንና፤ ነገ​ራ​ች​ንም ሁሉ ሥራ​ች​ን​ንም ማወ​ቅና መረ​ዳት በእጁ ነውና። 17ያለ ሐሰት ነዋሪ የሚ​ሆን የዕ​ው​ቀት ነገ​ርን ሰጠኝ፤ ዓለም ጸንቶ የሚ​ኖ​ር​በ​ት​ንም ሥር​ዐት፥ የፀ​ሐ​ይን፥ የጨ​ረ​ቃ​ንና የከ​ዋ​ክ​ብ​ት​ንም ሥራ አውቅ ዘንድ፤ 18የዘ​መ​ኑን መጀ​መ​ሪ​ያ​ው​ንና መጨ​ረ​ሻ​ውን፥ መካ​ከ​ሉ​ንም፥ የቀ​ኑን መመ​ላ​ለስ፥ የጊ​ዜ​ው​ንም መለ​ዋ​ወጥ፥ 19የዘ​መ​ና​ትን ዑደት፥ የከ​ዋ​ክ​ብ​ት​ንም አኗ​ኗር፥ 20የእ​ን​ስ​ሳ​ንም ጠባይ፥ የአ​ራ​ዊ​ት​ንም ቍጣ፥ የነ​ፋ​ሳ​ት​ንም ኀይል፥ የሰ​ው​ንም አሳብ፥ ዛፎ​ች​ንም ለይቶ ማወቅ፥ የሥ​ሮ​ች​ንም ተግ​ባር ኀይል አውቅ ዘንድ ሰጠኝ። 21የሥ​ራው ሁሉ አስ​ገኝ እርሱ ጥበ​ብን#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሥ​ራው ሁሉ አስ​ገኝ የሆ​ነች ጥበብ አስ​ተ​ም​ራ​ኛ​ለች” ይላል። አስ​ተ​ም​ሮ​ኛ​ልና የተ​ገ​ለ​ጸ​ው​ንና የተ​ሰ​ወ​ረ​ውን ሁሉ ዐወ​ቅሁ።
የጥ​በብ ጠባይ
22በእ​ር​ስዋ የማ​ስ​ተ​ዋል መን​ፈስ አለና፤ እር​ሱም ቅዱስ፥ በል​ደት ብቸኛ የሆነ፥ አንድ ሲሆን ሀብቱ ብዙ የሆነ፥ ረቂቅ፥ እን​ቅ​ስ​ቃ​ሴ​ውም የፈ​ጠነ፥ ቃሉ የሚ​ያ​ምር፥ ጠቢብ፥ ዕድ​ፈ​ትም የሌ​ለ​በት፥ የማ​ይ​ደ​ክም፥ ጥንት የሌ​ለው፥ ነዋሪ፥ ቸር​ነ​ትን የሚ​ወድ፥ ፈጣን፥ በጎ ነገ​ርን ለማ​ድ​ረግ የሚ​ከ​ለ​ክ​ለው የሌለ፥ 23ሰው ወዳጅ፥ የጥ​በብ ወዳ​ጅዋ፥ ዐዋቂ፥ እው​ነ​ተኛ፥ ግዳጅ የሌ​ለ​በት፥ ትዕ​ግ​ሥ​ተኛ፥ ሁሉን የሚ​ችል፥ ሁሉ​ንም የሚ​ጐ​በኝ፥ ንጹ​ሓ​ትና አስ​ተ​ዋ​ዮች፥ ረቂ​ቃ​ትም በሆኑ ነፍ​ሳት የሚ​ያ​ድር ነው። 24የጥ​በብ እን​ቅ​ስ​ቃ​ሴዋ ከእ​ን​ቅ​ስ​ቃሴ ሁሉ ይፈ​ጥ​ና​ልና። በሁ​ሉም ዘንድ በስ​ፋት ትመ​ላ​ለ​ሳ​ለች፤ ስለ ንጽ​ሕ​ና​ዋም ጽር​የት በሁሉ ትሄ​ዳ​ለች። 25የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የኀ​ይሉ እስ​ት​ን​ፋስ ናትና፥ አር​አ​ያው የታ​ወቀ፥ ክቡ​ርና ንጹሕ የሆነ የኀ​ያል አም​ላክ የክ​ብሩ መገ​ለጫ ናት። ስለ​ዚህ የሚ​ያ​ገ​ኛት ምንም ርኵ​ሰት የለም። 26የቀ​ዳ​ማዊ ብር​ሃን ነጸ​ብ​ራቅ ናትና፥ የማ​ት​ጨ​ልም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሥ​ራው መስ​ታ​ዋ​ትም ናትና፥ የቸ​ር​ነ​ቱም አር​ኣያ ናትና። 27አን​ዲት ስት​ሆን ሁሉን ማድ​ረግ ትች​ላ​ለች፤ ራስ​ዋም እየ​ኖ​ረች ሁሉን ታድ​ሳ​ለች፥ በየ​ት​ው​ል​ዱም በጻ​ድ​ቃን ሰው​ነት ትተ​ላ​ለ​ፋ​ለች፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ወዳ​ጆ​ችና ነቢ​ያቱ ታደ​ር​ጋ​ቸ​ዋ​ለች።
28እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከጥ​በብ ጋር ከሚ​ኖር ሰው በቀር የሚ​ወ​ድ​ደው የለ​ምና። 29እር​ስዋ ከፀ​ሐይ ይልቅ በመ​ልክ ታም​ራ​ለ​ችና፥ ከከ​ዋ​ክ​ብ​ትም ሥር​ዐት ሁሉ ትበ​ል​ጣ​ለች፤ ከብ​ር​ሃን ጋርም በም​ት​መ​ዘ​ን​በት ጊዜ በልጣ በፊቱ ትገ​ኛ​ለች። 30ብር​ሃ​ኑን ሌሊት ይለ​ው​ጠ​ዋ​ልና፥ ጥበ​ብን ግን ምንም ክፉ ነገር አይ​በ​ረ​ታ​ታ​ባ​ትም።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ