መዝሙር 113

113
መዝሙር 113
1ሃሌ ሉያ።#113፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ሲሆን፣ በሌሎች መዝሙራትም ይገኛል።
እግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤
እግዚአብሔርን ስም አወድሱ።
2ከአሁን እስከ ዘላለም፣
እግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።
3ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ድረስ፣
እግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።
4 እግዚአብሔር ከሕዝቦች ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ነው፤
ክብሩም ከሰማያት በላይ ነው።
5እንደ አምላካችን እንደ እግዚአብሔር
በላይ በዙፋኑ የተቀመጠ ማን ነው?
6በሰማይና በምድር ያሉትንስ ለማየት፣
ራሱን ወደ ታች ዝቅ የሚያደርግ ማን ነው?
7ድኻውን ከዐፈር ያነሣል፤
ችግረኛውን ከዐመድ ከፍ ከፍ ያደርጋል፤
8ከመኳንንትም እኩል ስፍራ ይሰጠዋል፤
ከሕዝቡም ሹማምት ጋራ ያስቀምጠዋል።
9መካኒቱን ሴት በቤት ያኖራታል፤
ደስተኛም የልጆች እናት ያደርጋታል።
ሃሌ ሉያ።

Currently Selected:

መዝሙር 113: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ