መዝሙር 123

123
መዝሙር 123
መዝሙረ መዓርግ።
1በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጥህ ሆይ፤
ዐይኖቼን ወደ አንተ አነሣለሁ።
2የባሪያዎች ዐይን ወደ ጌታቸው እጅ፣
የባሪያዪቱም ዐይን ወደ እመቤቷ እጅ እንደሚመለከት፣
ምሕረት እስከሚያደርግልን ድረስ፣
የእኛም ዐይኖች ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ይመለከታሉ።
3 እግዚአብሔር ሆይ፤ ንቀት በዝቶብናልና፣
ማረን፤ እባክህ ማረን።
4ነፍሳችን የቅንጡዎች ስድብ፣
የትዕቢተኞችም ንቀት እጅግ በዝቶባታል።

Currently Selected:

መዝሙር 123: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ