ትን​ቢተ ዳን​ኤል 13

13
ሶስና
1በባ​ቢ​ሎን የሚ​ኖር ስሙ ኢዮ​አ​ቄም የሚ​ባል አንድ ሰው ነበረ። 2የኬ​ል​ቅዩ ልጅ ስሟ ሶስና የም​ት​ባል ሚስት አግ​ብቶ ነበር። እጅ​ግም መልከ መል​ካ​ምና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈራ ነበ​ረች። 3ወላ​ጆ​ች​ዋም ደጋግ ሰዎች ነበሩ። ለል​ጃ​ቸ​ውም የሙ​ሴን ሕግ አስ​ተ​ም​ረ​ዋት ነበር። 4ባሏ ኢዮ​አ​ቄ​ምም እጅግ ባለ​ጸጋ ነበር፤ በቤ​ቱም አጠ​ገብ የተ​ክል ቦታ ነበ​ረው፤ ከሁሉ እርሱ ይከ​ብር ነበ​ርና አይ​ሁ​ድም ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።
5ኀጢ​አት ከባ​ቢ​ሎን፥ ሕዝ​ቡን እን​ጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋ​ለን ከሚሉ ግብ​ዞች መም​ህ​ራ​ንም እንደ ወጣች እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ እነ​ርሱ የተ​ና​ገ​ረ​ባ​ቸው ሁለት ግብ​ዞች መም​ህ​ራን በዚያ ወራት በሕ​ዝቡ መካ​ከል ታዩ። 6እነ​ር​ሱም በኢ​ዮ​አ​ቄም ቤት ያገ​ለ​ግሉ ነበር፥ የሚ​ፈ​ራ​ረዱ ሰዎ​ችም ሁሉ ወደ እርሱ#ግሪኩ “ወደ እነ​ርሱ” ይላል። ይመጡ ነበር።
7ሕዝቡ ሁሉ ወደ ቤታ​ቸው ከገቡ በኋላ ቀትር በሆነ ጊዜ ሶስና ወደ ባሏ ተክል ቦታ እየ​ገ​ባች በዚያ ትመ​ላ​ለስ ነበር። 8እነ​ዚ​ያም ሁለት መም​ህ​ራ​ን​በ​ዚያ እየ​ገ​ባች ስት​መ​ላ​ለስ ሁል​ጊዜ ያይ​ዋት ነበር። እር​ሷ​ንም ተመ​ኙ​አት። 9ልቡ​ና​ቸ​ው​ንም ለወጡ፤ ሰማ​ይ​ንም እን​ዳ​ያዩ ዐይ​ና​ቸ​ውን ከደኑ፤ እው​ነ​ተኛ ሕግ​ንም አላ​ሰ​ቡም። 10ሁለ​ቱም ሁሉ በፍ​ቅሯ ተነ​ደፉ፤ እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም በል​ቡ​ና​ቸው ያለ​ውን ነገር አል​ተ​ነ​ጋ​ገ​ሩም። 11ምኞ​ታ​ቸ​ውን መና​ገር አፍ​ረ​ዋ​ልና። ከእ​ር​ስ​ዋም ጋር ይተኙ ዘንድ ይፈ​ልጉ ነበር። 12ያገ​ኝ​ዋ​ትም ዘንድ ሁል​ጊዜ ይጠ​ብ​ቋት ነበር።
13አንዱ ሁለ​ተ​ኛ​ውን፥ “የምሣ ጊዜ ነውና ወደ ቤታ​ችን እን​ግባ አለው፤” 14እየ​ራ​ሳ​ቸ​ውም ተለ​ያ​ይ​ተው ሄዱ። ተመ​ል​ሰ​ውም በዚያ በአ​ን​ድ​ነት ተገ​ናኙ፤ ሁለ​ቱም ሁሉ ተያዩ፤ ያን​ጊ​ዜም ምኞ​ታ​ቸ​ውን ተነ​ጋ​ገሩ። እር​ስ​ዋ​ንም ብቻ​ዋን የሚ​ያ​ገ​ኙ​በ​ትን ጊዜ ተቃ​ጠሩ።
15ከዚህ በኋላ ቀን ሲጠ​ብ​ቋት ሶስና ሁል​ጊ​ዜም ትገባ እንደ ነበር ከሁ​ለቱ ደን​ገ​ጥ​ሮ​ችዋ ጋር ገባች፤ አል​ቧ​ትም ነበ​ርና በተ​ክል ቦታ ውስጥ ትታ​ጠብ ዘንድ ወደ​ደች። 16ተሰ​ው​ረ​ውም ከሚ​ጠ​ብ​ቋት ከሁ​ለቱ መም​ህ​ራን በቀር በዚያ ማንም አል​ነ​በ​ረም። 17ትታ​ጠ​ብም ዘንድ ደን​ገ​ጥ​ሮ​ች​ዋን ሽቱና ዘይት እን​ዲ​ያ​መ​ጡና የተ​ክ​ሉን ቦታ በር እን​ዲ​ዘጉ አዘ​ዘ​ቻ​ቸው። 18እነ​ር​ሱም እን​ዳ​ዘ​ዘ​ቻ​ቸው አደ​ረጉ፤ የተ​ክ​ሉ​ንም ቦታ በር ዘግ​ተው ያዘ​ዘ​ቻ​ቸ​ውን ያመጡ ዘንድ በስ​ርጥ ጎዳና ወጡ፤ የተ​ሰ​ወሩ እነ​ዚ​ያን መም​ህ​ራን ግን አላ​ዩ​አ​ቸ​ውም ነበር።
19እነ​ዚ​ያም ደን​ገ​ጥ​ሮች ከወጡ በኋላ ሁለቱ መም​ህ​ራን ተነ​ሥ​ተው ወደ እር​ስዋ ሮጡ። 20“እነሆ የተ​ክሉ ቦታ በር ተዘ​ግ​ት​ዋል፤ የሚ​ያ​የ​ንም የለም፤ ከአ​ንቺ ጋር እን​ተኛ ዘንድ እን​ወ​ዳ​ለ​ንና እሺ በዪን። 21ይህ ከአ​ል​ሆነ ግን ከአ​ንቺ ጋር ወንድ እንደ አገ​ኘን ተና​ግ​ረን እና​ጣ​ላ​ሻ​ለን፤ ስለ​ዚ​ህም ነገር ደን​ገ​ጥ​ሮ​ች​ሽን ከአ​ንቺ አስ​ወ​ጥ​ተሽ ሰደ​ድሽ” አሏት።
22ሶስ​ናም አለ​ቀ​ሰች፤ ”በሁ​ሉም ፈጽሜ ተቸ​ነ​ፍሁ፤ ባደ​ር​ገ​ውም እሞ​ታ​ለሁ፤ ባላ​ደ​ር​ገ​ውም አል​ድ​ንም፤ ከእ​ጃ​ቸው ማም​ለ​ጥ​ንም አል​ች​ልም። 23በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ከም​በ​ድል ኀጢ​አት ሳል​ሠራ በእ​ጃ​ችሁ መው​ደቅ ይሻ​ለ​ኛል” አለች። 24ሶስ​ናም ቃሏን አሰ​ምታ ጮኸች፤ እነ​ዚ​ያም መም​ህ​ራን ከእ​ርሷ ጋር ጮኹ።
25አን​ዱም ሮጦ የተ​ክ​ሉን ቦታ በር ከፈተ። 26በቤ​ት​ዋም ያሉ ሰዎች በተ​ክል ቦታW መካ​ከል ጩኸ​ትን ሰም​ተው ወጡ፤ ምንም እንደ ሆነ ያዩ ዘንድ በሥ​ርጥ ጎዳና ሮጡ። 27እነ​ዚ​ህም ሁለቱ መም​ህ​ራን ይህን ነገር በተ​ና​ገሩ ጊዜ በሶ​ስና እን​ደ​ዚህ ያለ ነገር ፈጽሞ ተሰ​ምቶ አያ​ው​ቅም ነበ​ርና ዘመ​ዶ​ች​ዋና አገ​ል​ጋ​ዮ​ችዋ እጅግ አፈሩ።
28በማ​ግ​ሥ​ቱም ሕዝቡ በባሏ በኢ​ዮ​አ​ቄም ዘንድ በተ​ሰ​በ​ሰቡ ጊዜ እነ​ዚያ ሁለት መም​ህ​ራን ሶስ​ናን ያስ​ገ​ድ​ሏት ዘንድ ከአ​መ​ፀኛ ልቡ​ና​ቸው ጋር መጡ። 29“በሕ​ዝቡ ሁሉ ፊት ያመ​ጧት ዘንድ ወደ ኢዮ​አ​ቄም ሚስት ወደ ሶስና ላኩ” አሉ ወደ​ሷም ላኩ​ባት። 30እር​ሷም ከእ​ና​ትና ከአ​ባ​ትዋ፥ ከል​ጆ​ች​ዋና ከዘ​መ​ዶ​ች​ዋም ሁሉ ጋር መጣች።
31ሶስ​ናም እጅግ ደመ ግቡና መልከ መል​ካም ነበ​ረች። 32እነ​ዚ​ያም ዐመ​ፀ​ኞች መም​ህ​ራን መል​ኳን ለመ​ጥ​ገብ ክን​ብ​ን​ቧን ይገ​ል​ጧት ዘንድ አዘዙ፤ ክን​ብ​ን​ቧ​ንም ገለ​ጧት። 33አባ​ት​ዋና እና​ትዋ፥ ቤተ ሰቦ​ች​ዋም፥ የሚ​ያ​ው​ቋ​ትም ሰዎች ሁሉ አለ​ቀ​ሱ​ላት።
34እነ​ዚ​ያም ሁለቱ መም​ህ​ራን በሕ​ዝቡ መካ​ከል ተነ​ሥ​ተው እጆ​ቻ​ቸ​ውን በራሷ ላይ አኖሩ። 35እሷ ግን ልቡ​ናዋ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ኗ​ልና እያ​ለ​ቀ​ሰች ወደ ሰማይ ተመ​ለ​ከ​ተች። 36እነ​ዚ​ያም መም​ህ​ራን፥ “ብቻ​ች​ንን በተ​ክል ቦታ ውስጥ ስን​መ​ላ​ለስ ይህች ሴት ከሁ​ለቱ ደን​ገ​ጥ​ሮ​ችዋ ጋር ገባች፤ ደን​ገ​ጥ​ሮ​ች​ዋም ልካ​ቸ​ዋ​ለ​ችና የተ​ክ​ሉን ቦታ በር ዘግ​ተው ሄዱ። 37ደን​ገ​ጥ​ሮ​ች​ዋ​ንም ከላ​ከ​ቻ​ቸው በኋላ አንድ ጎል​ማሳ ከተ​ሰ​ወ​ረ​በት መጥቶ ከእ​ር​ስዋ ጋር ተኛ። 38እኛም በዚያ ተክል ቦታ ዳርቻ ሆነን ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን አየን፤ ወደ እነ​ር​ሱም ሮጠን ሄድን፤ በአ​ን​ድ​ነ​ትም ተኝ​ተው አገ​ኘ​ና​ቸው። 39እኛም እር​ሱን መያዝ ተሳ​ነን፤ እሱ በር​ት​ቶ​ብ​ና​ልና አመ​ለ​ጠን፤ የተ​ክል ቦታ​ው​ንም በር ከፍቶ ወጣ። 40እር​ስ​ዋን ግን ያዝ​ናት፤ ሰው​የ​ውም ማን እንደ ሆነ ጠየ​ቅ​ናት፤ ነገር ግን አል​ነ​ገ​ረ​ች​ንም፤ ለዚ​ህም ነገር እኛ ምስ​ክ​ሮች ነን” አሉ። 41የሕ​ዝብ መም​ህ​ራን ነበ​ሩና ፈራ​ጆ​ችም ነበ​ሩና በአ​ደ​ባ​ባይ የተ​ሰ​በ​ሰቡ ሰዎች ነገ​ራ​ቸ​ውን አመ​ኗ​ቸው፤ ትሞ​ትም ዘንድ ፈረ​ዱ​ባት።
42ሶስ​ናም ቃሏን አሰ​ምታ ጮኸች፥ “ዘለ​ዓ​ለ​ማዊ የሆ​ንህ፥ የተ​ሰ​ወ​ረ​ውን የም​ታ​ውቅ፥ ከመ​ሆኑ በፊት ሁሉን የም​ታ​ውቅ አም​ላክ ሆይ! 43በሐ​ሰት እንደ መሰ​ከ​ሩ​ብኝ አንተ ታው​ቃ​ለህ፤ እነ​ዚህ መም​ህ​ራን ክፉ ነገ​ርን ስለ​አ​ደ​ረ​ጉ​ብኝ የሠ​ራ​ሁት ነገር ሳይ​ኖር እነሆ እሞ​ታ​ለሁ” አለች። 44እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቃሏን ሰማት። 45ይገ​ድ​ሏ​ትም ዘንድ ሲወ​ስ​ዷት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስሙ ዳን​ኤል የሚ​ባል የአ​ንድ ወጣት ልጅ ልቡ​ናን አነ​ሣሣ።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ቅዱስ መን​ፈ​ስን አነ​ሣሣ” ይላል። 46እር​ሱም፥ “እኔ ከዚች ሴት ደም ንጹሕ ነኝ” ብሎ ቃሉን አሰ​ምቶ ተና​ገረ።
47ሕዝ​ቡም ሁሉ ወደ እርሱ ተመ​ል​ሰው፥ “አንተ የም​ት​ና​ገ​ረው ይህ ነገር ምን​ድን ነው?” አሉ። 48ዳን​ኤ​ልም በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ቆሞ፥ “አላ​ዋ​ቂ​ዎች የም​ት​ሆኑ እና​ንት የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች! ሳት​መ​ረ​ምሩ፥ ነገ​ሩ​ንም ሳት​ረዱ በእ​ስ​ራ​ኤል ሴት ልጅ ላይ እን​ደ​ዚህ ትፈ​ር​ዳ​ላ​ች​ሁን? 49እነ​ዚህ መም​ህ​ራን በሐ​ሰት መስ​ክ​ረ​ው​ባ​ታ​ልና ወደ አደ​ባ​ባይ ተመ​ለሱ” አላ​ቸው። 50ሕዝ​ቡም ሁሉ እየ​ሮጡ ወደ አደ​ባ​ባይ ተመ​ለሱ፤ አለ​ቆ​ችም ዳን​ኤ​ልን፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አን​ተን አል​ቆ​ሃ​ልና በመ​ካ​ከ​ላ​ችን ተቀ​ም​ጠህ ንገ​ረን” አሉት። 51ዳን​ኤ​ልም፥ “እየ​ራ​ሳ​ቸው አራ​ር​ቃ​ችሁ አቁ​ሟ​ቸው፤ እኔም ልመ​ር​ም​ራ​ቸው” አላ​ቸው። 52እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ው​ንም አራ​ር​ቀው አቆ​ሟ​ቸው፤ እር​ሱም አን​ዱን ጠርቶ፥ “አንተ በክ​ፋት ያረ​ጀህ፥ ቀድሞ የሠ​ራ​ሃ​ቸው ኀጢ​አ​ቶ​ችህ ደረ​ሱ​ብህ። 53የሐ​ሰት ፍር​ድን ፈር​ደ​ሃ​ልና ጻድ​ቁ​ንና ንጹ​ሑን አት​ግ​ደል ብሎ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቢከ​ለ​ክል በደ​ለ​ኛ​ውን አዳ​ንህ፤ ንጹ​ሑ​ንም ገደ​ልህ። 54አሁ​ንም ይህ​ቺን ሴት ከአ​የ​ሃት ሁለ​ቱን ሁሉ በምን ዐይ​ነት ዛፍ ሥር ሲጫ​ወቱ አየህ? ንገ​ረኝ” አለው “በኮክ ዛፍ ሥር ሲጫ​ወቱ አየ​ኋ​ቸው” አለ።
55ዳን​ኤ​ልም፥ “በእ​ው​ነት ሐሰ​ትን ተና​ገ​ርህ፤ ደምህ በራ​ስህ ላይ ነው፤ ከመ​ካ​ከ​ልህ ይሰ​ነ​ጥ​ቅህ ዘንድ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​አክ እነሆ፥ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ታዘዘ” አለው። 56እር​ሱ​ንም እልፍ አደ​ረ​ገው፤ ሁለ​ተ​ኛ​ው​ንም ያመ​ጡት ዘንድ አዘዘ፤ አመ​ጡ​ትም፤ “አንተ የይ​ሁዳ ዘር ያይ​ደ​ለህ የከ​ነ​ዓን ዘር ነህ፤ ውበት አሳ​ተህ፤ ክፉ ፈቃ​ድም ልቡ​ና​ህን ገለ​በ​ጠው። 57እር​ስዋ እና​ን​ተን መከ​ራ​ከር አል​ቻ​ለ​ች​ምና፥ የይ​ሁዳ ሴት ልጅ እና​ን​ተን ፈር​ታ​ለ​ችና፥ ዐመ​ፃ​ች​ሁ​ንም ታግ​ሣ​ለ​ችና የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ሴት ልጅ እን​ዲህ ታደ​ር​ጓ​ታ​ላ​ች​ሁን። 58አሁ​ንም ሁለቱ ሲጫ​ወቱ ያየ​ህ​በት ዛፍ ምን​ድን ነው? ንገ​ረኝ” አለው። እር​ሱም፥ “ሮማን በሚ​ባል ዛፍ ሥር አየ​ኋት” አለው።
59ዳን​ኤ​ልም፥ “አን​ተም በእ​ው​ነት ሐሰ​ትን ተና​ገ​ርህ፤ ደም​ህም በራ​ስህ ላይ ነው፤ በሰ​ይፍ ከሁ​ለት ይሰ​ነ​ጥ​ቅህ ዘንድ፥ ፈጽ​ሞም ያጠ​ፋህ ዘንድ እነሆ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​አክ ይጠ​ብ​ቅ​ሃል” አለው።
60ሕዝ​ቡም ሁሉ ቃላ​ቸ​ውን አሰ​ም​ተው ጮኹ፤ ያመ​ነ​ች​በት፥ ሶስ​ናን#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሚ​ያ​ም​ኑ​በ​ትን ሁሉ የሚ​ያ​ድን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ...” ይላል። ያዳ​ናት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አመ​ሰ​ገኑ። 61ከቃ​ላ​ቸው የተ​ነሣ ዳን​ኤል ነቅ​ፏ​ቸ​ዋ​ልና፥ ምስ​ክ​ር​ነ​ታ​ቸ​ው​ንም ሐሰት አድ​ር​ጎ​ባ​ቸ​ዋ​ልና በእ​ነ​ዚያ በሁ​ለቱ መም​ህ​ራን ላይ በጠ​ላ​ት​ነት ተነ​ሡ​ባ​ቸው። 62እንደ ሙሴም ሕግ በባ​ል​ን​ጀ​ራ​ቸው ላይ ክፉ እንደ አደ​ረጉ በእ​ነ​ር​ሱም ላይ አደ​ረ​ጉ​ባ​ቸው። ገደ​ሉ​አ​ቸ​ውም፤ በዚ​ያ​ችም ቀን ንጹሕ ደምን አዳኑ።
63በእ​ርሷ ላይ ክፉ ሥራ አል​ተ​ገ​ኘ​ምና ስለ ልጃ​ቸው ስለ ሶስና ኬል​ቅ​ዩና ሚስቱ ከባ​ልዋ ከኢ​ዮ​አ​ቄ​ምና ከዘ​መ​ዶ​ችዋ ሁሉ ጋር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ገ​ኑት። 64ዳን​ኤ​ልም ከዚ​ያች ቀን ጀምሮ ሁል​ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በሕ​ዝቡ ፊት ገናና ሆነ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ