ትንቢተ ዳንኤል 5
5
ብልጣሶር ለመኳንንቱ ግብር እንደ አበላ
1ንጉሡ ብልጣሶር ለሺህ መኳንንቱ ትልቅ ግብዣ አደረገ፤ ለሺሁም የወይን ጠጅ ያጠጣ ነበር። 2ብልጣሶርም የወይን ጠጅ በጠጣ ጊዜ ንጉሡና መኳንንቱ፥ ሚስቶቹና ቁባቶቹ ይጠጡባቸው ዘንድ፥ “አባቴ ናቡከደነፆር በኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ ያመጣቸውን የወርቁንና የብሩን ዕቃዎች አምጡ” ብሎ አዘዘ። 3ያን ጊዜም በኢየሩሳሌም ከነበረው ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የመጡትን የወርቁንና የብሩን ዕቃዎች አመጡ፤ ንጉሡና መኳንንቱም፥ ሚስቶቹና ቁባቶቹም ጠጡባቸው። 4የወይን ጠጅም እየጠጡ ከወርቅና ከብር፥ ከናስና ከብረት፥ ከእንጨትና ከድንጋይ የተሠሩትን አማልክት አመሰገኑ።
5በዚያም ሰዓት የሰው እጅ ጣት ወጥታ በንጉሡ ቤት በተለሰነው ግንብ ላይ በመቅረዙ አንጻር ጻፈች፤ ንጉሡም የሰው ጣት ስትጽፍ አየ። 6ያን ጊዜም የንጉሡ ፊት ተለወጠ፤ ልቡም ታወከ፤ የወገቡም ጅማቶች ተፈቱ፤ ጕልበቶቹም ተብረከረኩ። 7ንጉሡም አስማተኞቹንና ከለዳውያኑን፥ ቃላተኞቹንም ያገቡ ዘንድ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ንጉሡም የባቢሎንን ጠቢባን፥ “ይህን ጽሕፈት ያነበበ፥ ፍቺውንም የነገረኝ ሐምራዊ ግምጃ ይለብሳል፤ የወርቅም ማርዳ በአንገቱ አስርለታለሁ፤ በመንግሥቴም ላይ ሦስተኛ ገዥ አድርጌ እሾመዋለሁ” ብሎ ተናገረ። 8የዚያን ጊዜም የንጉሡ ጠቢባን ሁሉ ገቡ፤ ነገር ግን ጽሕፈቱን ያነብቡ ዘንድ፥ ፍቺውንም ለንጉሡ ይነግሩ ዘንድ አልቻሉም። 9ንጉሡም ብልጣሶር እጅግ ደነገጠ፤ ፊቱም ተለወጠበት፤ መኳንንቱም ተደናገጡ።
10ንግሥቲቱም የንጉሡንና የመኳንንቱን ቃል#“የንጉሡንና የመኳንንቱን ቃል” የሚለው በዕብ. ብቻ። ሰምታ ወደ ግብዣ ቤት ገባች፤ እንዲህም አለች፥ “ንጉሥ ሆይ! ለዘለዓለም ኑር፤ አሳብህ አያስቸግርህ፤ ፊትህም አይለወጥ። 11የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያለበት ሰው በመንግሥትህ ውስጥ አለ፤ በአባትህም ዘመን እንደ አማልክት ጥበብ ያለ ጥበብና ማስተዋል፥ ዕውቀትም ተገኘበት፤ አባትህ ንጉሡ ናቡከደነፆር የሕልም ተርጓሚዎችና የአስማተኞች፥ የከለዳውያንና የቃላተኞች አለቃ አድርጎ ሾመው። 12መልካም መንፈስ፥ ዕውቀትም፥ ማስተዋልም፥ ሕልምንም መተርጐም፥ እንቆቅልሽንም መግለጥ፥ የታተመውንም መፍታት በእርሱ ተገኝቶአልና፤ እርሱም ንጉሡ ስሙን ብልጣሶር ብሎ የሰየመው ዳንኤል ነው። አሁንም እርሱ ይጠራ፤ እርሱም ፍቺውን ይነግርሃል።”
13የዚያን ጊዜም ዳንኤል ወደ ንጉሡ ፊት ገባ፤ ንጉሡም ተናገረው፤ ዳንኤልንም እንዲህ አለው፥ “ንጉሡ አባቴ ከይሁዳ ከማረካቸው ከይሁዳ ምርኮኞች ልጆች የሆንህ ዳንኤል አንተ ነህን? 14የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ እንደ አለብህ፥ ዕውቀትና ማስተዋልም፥ ሕልምንም መተርጐም እንደ ተገኘብህ ስለ አንተ ሰምቻለሁ። 15አሁንም ይህን ጽሕፈት ያነብቡ ዘንድ፥ ፍቺውንም ይነግሩኝ ዘንድ ጠንቋዮችና ፈላስፎች፥ ጠቢባንና ሟርተኞችም ወደ እኔ ገብተው ነበር፤ ነገር ግን የነገሩን ፍቺ ይነግሩኝ ዘንድ አልቻሉም። 16አንተ ግን ፍቺን ትሰጥ ዘንድ፥ የታተመውንም ትፈታ ዘንድ እንድትችል ሰምቻለሁ፤ አሁንም ጽሕፈቱን ታነብብ ዘንድ፥ ፍቺውንም ትነግረኝ ዘንድ ብትችል፥ ሐምራዊ ግምጃ ትለብሳለህ፤ የወርቅም ማርዳ በአንገትህ ዙሪያ አስርልሃለሁ፤ አንተም በመንግሥቴ ላይ ሦስተኛ ገዥ ትሆናለህ።” 17የዚያን ጊዜም ዳንኤል መለሰ፤ በንጉሡም ፊት እንዲህ አለ፥ “ስጦታህ ለአንተ ይሁን፤ የመንግሥትህንም ሢሶ ለሌላ ስጥ፤ ነገር ግን ጽሕፈቱን ለንጉሡ አነብባለሁ፤ ፍቺውንም እነግርሃለሁ። 18ንጉሥ ሆይ! ልዑል አምላክ ለአባትህ ለናቡከደነፆር መንግሥትንና ታላቅነትን፥ ክብርንና ግርማን ሰጠው። 19ስለ ሰጠው ታላቅነት ወገኖችና አሕዛብ፥ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ሁሉ በፊቱ ይንቀጠቀጡና ይፈሩ ነበር፤ የፈቀደውን ይገድል፥ የፈቀደውንም በሕይወት ያኖር ነበር፤ የፈቀደውንም ያነሣ፥ የፈቀደውንም ያዋርድ ነበር። 20ልቡ ግን በታበየ ጊዜ፥ በኵራትም ያደርግ ዘንድ መንፈሱ በጠነከረ ጊዜ፥ ከመንግሥቱ ዙፋን ተዋረደ፤ ክብሩም ተለየው። 21ልዑል አምላክም የሰዎችን መንግሥት እንዲገዛ፥ ለሚወድደውም እንዲሰጠው እስኪያውቅ ደረስ ከሰው ልጆች ተለይቶ ተሰደደ፥ ልቡም እንደ አውሬ ልብ ሆነ፤ መኖሪያውም ከምድረ በዳ አህዮች ጋር ነበረ፤ እንደ በሬም ሣር በላ፤ አካሉም በሰማይ ጠል ረሰረሰ። 22ብልጣሶር ሆይ! አንተ ልጁ ስትሆን በእግዚአብሔር ፊት ልብህን አላዋረድህም፤ ይህንም ሁሉ አላወቅህም። 23በሰማይ አምላክ በእግዚአብሔር ላይ ኰራህ፤ የመቅደሱንም ዕቃዎች በፊትህ አመጡ፤ አንተም መኳንንትህም፥ ሚስቶችህም፥ ቁባቶችህም የወይን ጠጅ ጠጣችሁባቸው፤ ከብርና ከወርቅም፥ ከናስና ከብረትም፥ ከእንጨትና ከድንጋይም የተሠሩትን፥ የማያዩትንና የማይሰሙትንም፥ የማያውቁትንም አማልክት አመሰገንህ፤ ትንፋሽህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ ግን አላመሰገንኸውም። 24ስለዚህም ይህ የሰው እጅ ጣት ከእርሱ ዘንድ ተልኳል፤ ይህም ጽሕፈት ተጽፎአል።
25“የተጻፈውም ጽሕፈት፦ ማኔ፥ ቴቄል፥ ፋሬስ ይላል። 26የነገሩም ፍቺ ይህ ነው፤ ማኔ ማለት፥ እግዚአብሔር መንግሥትህን ቈጠራት፤ ፈጸማትም ማለት ነው። 27ቴቄል ማለት፥ በሚዛን ተመዘነች፤ ቀልላም ተገኘች#ዕብ. “በሚዛን ተመዝነህ ቀልለህም ተገኘህ” ይላል። ማለት ነው። 28ፋሬስ ማለት፥ መንግሥትህ ተከፈለች፤ ለሜዶንና ለፋርስ ሰዎችም ተሰጠች” ማለት ነው።
29የዚያን ጊዜም ብልጣሶር ለዳንኤል ሐምራዊ ግምጃ እንዲያለብሱት፥ የወርቅ ማርዳም በአንገቱ ዙሪያ እንዲያደርጉለት አዘዘ፤ በመንግሥትም ላይ ሦስተኛ ገዥ እንዲሆን ዐዋጅ አስነገረ።
30በዚያም ሌሊት የከለዳውያን ንጉሥ ብልጣሶር ተገደለ። 31ሜዶናዊውም ዳርዮስ በእርሱ ፋንታ ነገሠ። ዕድሜውም ስድሳ ሁለት ዓመት ነበረ።
Currently Selected:
ትንቢተ ዳንኤል 5: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
ትንቢተ ዳንኤል 5
5
ብልጣሶር ለመኳንንቱ ግብር እንደ አበላ
1ንጉሡ ብልጣሶር ለሺህ መኳንንቱ ትልቅ ግብዣ አደረገ፤ ለሺሁም የወይን ጠጅ ያጠጣ ነበር። 2ብልጣሶርም የወይን ጠጅ በጠጣ ጊዜ ንጉሡና መኳንንቱ፥ ሚስቶቹና ቁባቶቹ ይጠጡባቸው ዘንድ፥ “አባቴ ናቡከደነፆር በኢየሩሳሌም ከነበረው ቤተ መቅደስ ያመጣቸውን የወርቁንና የብሩን ዕቃዎች አምጡ” ብሎ አዘዘ። 3ያን ጊዜም በኢየሩሳሌም ከነበረው ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የመጡትን የወርቁንና የብሩን ዕቃዎች አመጡ፤ ንጉሡና መኳንንቱም፥ ሚስቶቹና ቁባቶቹም ጠጡባቸው። 4የወይን ጠጅም እየጠጡ ከወርቅና ከብር፥ ከናስና ከብረት፥ ከእንጨትና ከድንጋይ የተሠሩትን አማልክት አመሰገኑ።
5በዚያም ሰዓት የሰው እጅ ጣት ወጥታ በንጉሡ ቤት በተለሰነው ግንብ ላይ በመቅረዙ አንጻር ጻፈች፤ ንጉሡም የሰው ጣት ስትጽፍ አየ። 6ያን ጊዜም የንጉሡ ፊት ተለወጠ፤ ልቡም ታወከ፤ የወገቡም ጅማቶች ተፈቱ፤ ጕልበቶቹም ተብረከረኩ። 7ንጉሡም አስማተኞቹንና ከለዳውያኑን፥ ቃላተኞቹንም ያገቡ ዘንድ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ንጉሡም የባቢሎንን ጠቢባን፥ “ይህን ጽሕፈት ያነበበ፥ ፍቺውንም የነገረኝ ሐምራዊ ግምጃ ይለብሳል፤ የወርቅም ማርዳ በአንገቱ አስርለታለሁ፤ በመንግሥቴም ላይ ሦስተኛ ገዥ አድርጌ እሾመዋለሁ” ብሎ ተናገረ። 8የዚያን ጊዜም የንጉሡ ጠቢባን ሁሉ ገቡ፤ ነገር ግን ጽሕፈቱን ያነብቡ ዘንድ፥ ፍቺውንም ለንጉሡ ይነግሩ ዘንድ አልቻሉም። 9ንጉሡም ብልጣሶር እጅግ ደነገጠ፤ ፊቱም ተለወጠበት፤ መኳንንቱም ተደናገጡ።
10ንግሥቲቱም የንጉሡንና የመኳንንቱን ቃል#“የንጉሡንና የመኳንንቱን ቃል” የሚለው በዕብ. ብቻ። ሰምታ ወደ ግብዣ ቤት ገባች፤ እንዲህም አለች፥ “ንጉሥ ሆይ! ለዘለዓለም ኑር፤ አሳብህ አያስቸግርህ፤ ፊትህም አይለወጥ። 11የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያለበት ሰው በመንግሥትህ ውስጥ አለ፤ በአባትህም ዘመን እንደ አማልክት ጥበብ ያለ ጥበብና ማስተዋል፥ ዕውቀትም ተገኘበት፤ አባትህ ንጉሡ ናቡከደነፆር የሕልም ተርጓሚዎችና የአስማተኞች፥ የከለዳውያንና የቃላተኞች አለቃ አድርጎ ሾመው። 12መልካም መንፈስ፥ ዕውቀትም፥ ማስተዋልም፥ ሕልምንም መተርጐም፥ እንቆቅልሽንም መግለጥ፥ የታተመውንም መፍታት በእርሱ ተገኝቶአልና፤ እርሱም ንጉሡ ስሙን ብልጣሶር ብሎ የሰየመው ዳንኤል ነው። አሁንም እርሱ ይጠራ፤ እርሱም ፍቺውን ይነግርሃል።”
13የዚያን ጊዜም ዳንኤል ወደ ንጉሡ ፊት ገባ፤ ንጉሡም ተናገረው፤ ዳንኤልንም እንዲህ አለው፥ “ንጉሡ አባቴ ከይሁዳ ከማረካቸው ከይሁዳ ምርኮኞች ልጆች የሆንህ ዳንኤል አንተ ነህን? 14የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ እንደ አለብህ፥ ዕውቀትና ማስተዋልም፥ ሕልምንም መተርጐም እንደ ተገኘብህ ስለ አንተ ሰምቻለሁ። 15አሁንም ይህን ጽሕፈት ያነብቡ ዘንድ፥ ፍቺውንም ይነግሩኝ ዘንድ ጠንቋዮችና ፈላስፎች፥ ጠቢባንና ሟርተኞችም ወደ እኔ ገብተው ነበር፤ ነገር ግን የነገሩን ፍቺ ይነግሩኝ ዘንድ አልቻሉም። 16አንተ ግን ፍቺን ትሰጥ ዘንድ፥ የታተመውንም ትፈታ ዘንድ እንድትችል ሰምቻለሁ፤ አሁንም ጽሕፈቱን ታነብብ ዘንድ፥ ፍቺውንም ትነግረኝ ዘንድ ብትችል፥ ሐምራዊ ግምጃ ትለብሳለህ፤ የወርቅም ማርዳ በአንገትህ ዙሪያ አስርልሃለሁ፤ አንተም በመንግሥቴ ላይ ሦስተኛ ገዥ ትሆናለህ።” 17የዚያን ጊዜም ዳንኤል መለሰ፤ በንጉሡም ፊት እንዲህ አለ፥ “ስጦታህ ለአንተ ይሁን፤ የመንግሥትህንም ሢሶ ለሌላ ስጥ፤ ነገር ግን ጽሕፈቱን ለንጉሡ አነብባለሁ፤ ፍቺውንም እነግርሃለሁ። 18ንጉሥ ሆይ! ልዑል አምላክ ለአባትህ ለናቡከደነፆር መንግሥትንና ታላቅነትን፥ ክብርንና ግርማን ሰጠው። 19ስለ ሰጠው ታላቅነት ወገኖችና አሕዛብ፥ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ሁሉ በፊቱ ይንቀጠቀጡና ይፈሩ ነበር፤ የፈቀደውን ይገድል፥ የፈቀደውንም በሕይወት ያኖር ነበር፤ የፈቀደውንም ያነሣ፥ የፈቀደውንም ያዋርድ ነበር። 20ልቡ ግን በታበየ ጊዜ፥ በኵራትም ያደርግ ዘንድ መንፈሱ በጠነከረ ጊዜ፥ ከመንግሥቱ ዙፋን ተዋረደ፤ ክብሩም ተለየው። 21ልዑል አምላክም የሰዎችን መንግሥት እንዲገዛ፥ ለሚወድደውም እንዲሰጠው እስኪያውቅ ደረስ ከሰው ልጆች ተለይቶ ተሰደደ፥ ልቡም እንደ አውሬ ልብ ሆነ፤ መኖሪያውም ከምድረ በዳ አህዮች ጋር ነበረ፤ እንደ በሬም ሣር በላ፤ አካሉም በሰማይ ጠል ረሰረሰ። 22ብልጣሶር ሆይ! አንተ ልጁ ስትሆን በእግዚአብሔር ፊት ልብህን አላዋረድህም፤ ይህንም ሁሉ አላወቅህም። 23በሰማይ አምላክ በእግዚአብሔር ላይ ኰራህ፤ የመቅደሱንም ዕቃዎች በፊትህ አመጡ፤ አንተም መኳንንትህም፥ ሚስቶችህም፥ ቁባቶችህም የወይን ጠጅ ጠጣችሁባቸው፤ ከብርና ከወርቅም፥ ከናስና ከብረትም፥ ከእንጨትና ከድንጋይም የተሠሩትን፥ የማያዩትንና የማይሰሙትንም፥ የማያውቁትንም አማልክት አመሰገንህ፤ ትንፋሽህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ ግን አላመሰገንኸውም። 24ስለዚህም ይህ የሰው እጅ ጣት ከእርሱ ዘንድ ተልኳል፤ ይህም ጽሕፈት ተጽፎአል።
25“የተጻፈውም ጽሕፈት፦ ማኔ፥ ቴቄል፥ ፋሬስ ይላል። 26የነገሩም ፍቺ ይህ ነው፤ ማኔ ማለት፥ እግዚአብሔር መንግሥትህን ቈጠራት፤ ፈጸማትም ማለት ነው። 27ቴቄል ማለት፥ በሚዛን ተመዘነች፤ ቀልላም ተገኘች#ዕብ. “በሚዛን ተመዝነህ ቀልለህም ተገኘህ” ይላል። ማለት ነው። 28ፋሬስ ማለት፥ መንግሥትህ ተከፈለች፤ ለሜዶንና ለፋርስ ሰዎችም ተሰጠች” ማለት ነው።
29የዚያን ጊዜም ብልጣሶር ለዳንኤል ሐምራዊ ግምጃ እንዲያለብሱት፥ የወርቅ ማርዳም በአንገቱ ዙሪያ እንዲያደርጉለት አዘዘ፤ በመንግሥትም ላይ ሦስተኛ ገዥ እንዲሆን ዐዋጅ አስነገረ።
30በዚያም ሌሊት የከለዳውያን ንጉሥ ብልጣሶር ተገደለ። 31ሜዶናዊውም ዳርዮስ በእርሱ ፋንታ ነገሠ። ዕድሜውም ስድሳ ሁለት ዓመት ነበረ።