ትን​ቢተ ዳን​ኤል 9

9
የዳ​ን​ኤል ጸሎት
1በከ​ለ​ዳ​ው​ያን መን​ግ​ሥት ላይ በነ​ገሠ፥ ከሜ​ዶን ዘር በነ​በረ በአ​ሕ​ሻ​ዊ​ሮስ ልጅ በዳ​ር​ዮስ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት፥ 2በነ​ገሠ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት እኔ ዳን​ኤል በሰባ ዓመት የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ጥፋት እን​ደ​ሚ​ፈ​ጸም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በነ​ቢዩ ኤር​ም​ያስ የተ​ና​ገ​ረው ቃል በተ​ጻ​ፈ​በት መጽ​ሐፍ ያለ​ውን የዘ​መ​ኑን ቍጥር ዐወ​ቅሁ።
3ማቅ ለብሼ፥ በአ​መ​ድም ላይ ሆኜ ስጾም እጸ​ል​ይና እለ​ምን ዘንድ ፊቴን ወደ ጌታ ወደ አም​ላክ አቀ​ናሁ። 4ወደ አም​ላ​ኬም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸለ​ይሁ፤ ተና​ዝ​ዤም እን​ዲህ አልሁ፥ “ጌታ ሆይ! ከሚ​ወ​ድ​ዱ​ህና ትእ​ዛ​ዝ​ህን ከሚ​ፈ​ጽሙ ጋር ቃል ኪዳ​ን​ንና ምሕ​ረ​ትን የም​ት​ጠ​ብቅ ታላ​ቅና የም​ታ​ስ​ፈራ አም​ላክ ሆይ! 5ኀጢ​አ​ትን ሠር​ተ​ናል፥ በድ​ለ​ን​ማል፤ ክፋ​ት​ንም አድ​ር​ገ​ናል፤ ዐም​ፀ​ን​ማል፤ ከት​እ​ዛ​ዝ​ህና ከፍ​ር​ድ​ህም ፈቀቅ ብለ​ናል፤ 6በስ​ም​ህም ለነ​ገ​ሥ​ታ​ቶ​ቻ​ች​ንና ለአ​ለ​ቆ​ቻ​ችን፥ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ንም፥ ለሀ​ገ​ሩም ሕዝብ ሁሉ የተ​ና​ገ​ሩ​ትን ባሪ​ያ​ዎ​ች​ህን ነቢ​ያ​ትን አል​ሰ​ማ​ንም። 7ጌታ ሆይ! ጽድቅ ለአ​ንተ ነው፤ እንደ ዛሬም ለእኛ ለይ​ሁዳ ሰዎ​ችና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ለሚ​ቀ​መጡ፥ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ በቅ​ር​ብና በሩ​ቅም ላሉት አን​ተን በበ​ደ​ሉ​በት በበ​ደ​ላ​ቸው ምክ​ን​ያት በበ​ተ​ን​ህ​በት ሀገር ሁሉ የፊት እፍ​ረት ነው። 8ጌታ ሆይ!#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ጽድ​ቃ​ችን በአ​ንተ ላይ ነው” የሚል ይጨ​ም​ራል። በአ​ንተ ላይ ኀጢ​አት ስለ ሠራን ለእ​ኛና ለነ​ገ​ሥ​ታ​ቶ​ቻ​ችን፥ ለአ​ለ​ቆ​ቻ​ች​ንና ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ንም የፊት እፍ​ረት ነው። 9ለጌታ ለአ​ም​ላ​ካ​ችን ምሕ​ረ​ትና ይቅ​ርታ ነው፤ በእ​ርሱ ላይ ዐም​ፀ​ና​ልና። 10በባ​ሪ​ያ​ዎ​ቹም በነ​ቢ​ያት እጅ በፊ​ታ​ችን በአ​ኖ​ረው በሕጉ እን​ሄድ ዘንድ የአ​ም​ላ​ካ​ች​ንን የግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል አል​ሰ​ማ​ን​ምና። 11እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ ሕግ​ህን ተላ​ል​ፈ​ዋል፤ ቃል​ህ​ንም መስ​ማ​ትን እንቢ ብለ​ዋል፤ በእ​ርሱ ላይ ኀጢ​አት ሠር​ተ​ና​ልና መር​ገ​ምና በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሪያ በሙሴ ሕግ የተ​ጻ​ፈው መሐላ መጣ​ብን። 12እጅግ ክፉ ነገ​ር​ንም በእኛ ላይ በማ​ም​ጣቱ በላ​ያ​ች​ንና በእኛ ዘንድ በተ​ሾ​ሙት ፈራ​ጆ​ቻ​ችን ላይ የተ​ና​ገ​ረ​ውን ቃል አጸና፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ላይ እንደ ተደ​ረ​ገው ያለ ነገር ከቶ ከሰ​ማይ ሁሉ በታች አል​ተ​ደ​ረ​ገም። 13በሙ​ሴም ሕግ እንደ ተጻፈ ይህ ክፉ ነገር ሁሉ መጣ​ብን፤ ከኀ​ጢ​አ​ታ​ችን እን​መ​ለስ፤ እው​ነ​ት​ህ​ንም እና​ስብ ዘንድ ወደ አም​ላ​ካ​ችን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት አል​ለ​መ​ን​ንም። 14ስለ​ዚ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክፉ ነገ​ርን በእኛ ላይ ፈጥኖ አመጣ፤ አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ሠ​ራው ሥራ ሁሉ ጻድቅ ነውና፤ እኛም ቃሉን አል​ሰ​ማ​ን​ምና። 15አሁ​ንም ሕዝ​ብ​ህን ከግ​ብፅ ምድር በበ​ረ​ታች እጅ ያወ​ጣህ፥ እንደ ዛሬም ቀን ስምን ለአ​ንተ ያደ​ረ​ግህ ጌታ አም​ላ​ካ​ችን ሆይ! ኀጢ​አ​ትን ሠር​ተ​ናል፤ ክፋ​ት​ንም አድ​ር​ገ​ናል። 16ጌታ ሆይ! በፍ​ጹም ቸር​ነ​ትህ ቍጣ​ህ​ንና መቅ​ሠ​ፍ​ት​ህን ከከ​ተ​ማህ ከኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና ከተ​ቀ​ደ​ሰው ተራ​ራህ መልስ፤ ስለ ኀጢ​አ​ታ​ች​ንና ስለ አባ​ቶ​ቻ​ችን በደል ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና ሕዝ​ብህ በዙ​ሪ​ያ​ችን ላሉት ሁሉ መሰ​ደ​ቢያ ሆነ​ዋ​ልና። 17አሁ​ንም አም​ላ​ካ​ችን ሆይ! የባ​ሪ​ያ​ህን ጸሎ​ትና ልመ​ና​ውን ስማ፤ ጌታ ሆይ! በፈ​ረ​ሰው በመ​ቅ​ደ​ስህ ላይ ስለ አንተ ስትል ፊት​ህን አብራ። 18አም​ላኬ ሆይ! በፊ​ትህ የም​ን​ለ​ምን ስለ ብዙ ምሕ​ረ​ትህ ነው እንጂ ስለ ጽድ​ቃ​ችን አይ​ደ​ለ​ምና ጆሮ​ህን አዘ​ን​ብ​ለህ ስማ፤ ዐይ​ን​ህ​ንም ገል​ጠህ ጥፋ​ታ​ች​ን​ንና ስምህ የተ​ጠ​ራ​ባ​ትን ከተማ ተመ​ል​ከት። 19አቤቱ! ስማ፤ አቤቱ፥ ይቅር በል፤ አቤቱ! አድ​ም​ጥና አድ​ርግ፤ አም​ላኬ ሆይ! ስምህ በከ​ተ​ማ​ህና በሕ​ዝ​ብህ ላይ ተጠ​ር​ቶ​አ​ልና ስለ ራስህ አት​ዘ​ግይ።”
20እኔም ገና ስና​ገ​ርና ስጸ​ልይ፥ በኀ​ጢ​አ​ቴና በሕ​ዝ​ቤም በእ​ስ​ራ​ኤል ኀጢ​አት ስና​ዘዝ፥ በአ​ም​ላ​ኬም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ስለ ተቀ​ደ​ሰው ስለ አም​ላኬ ተራራ ይቅ​ር​ታን ስጠ​ይቅ፥ 21ገናም በጸ​ሎት ስና​ገር አስ​ቀ​ድሜ በራ​እይ አይ​ችው የነ​በ​ረው ሰው ገብ​ር​ኤል እነሆ እየ​በ​ረረ መጣ፤ በማ​ታም መሥ​ዋ​ዕት ጊዜ ዳሰ​ሰኝ። 22አስ​ተ​ማ​ረ​ኝም፤ ተና​ገ​ረ​ኝም፤ እን​ዲ​ህም አለ፥ “ዳን​ኤል ሆይ! ጥበ​ብ​ንና ማስ​ተ​ዋ​ልን እሰ​ጥህ ዘንድ አሁን መጥ​ቻ​ለሁ። 23አንተ እጅግ የተ​ወ​ደ​ድህ ሰው ነህና በል​መ​ናህ መጀ​መ​ሪያ ላይ ቃል ወጥ​ቶ​አል፤ እኔም እነ​ግ​ርህ ዘንድ መጥ​ቻ​ለሁ፤ አሁ​ንም ነገ​ሩን መር​ምር፤ ራእ​ዩ​ንም አስ​ተ​ውል።
24“ዐመ​ፃን ይጨ​ርስ፥ ኀጢ​አ​ት​ንም ይፈ​ጽም፥ በደ​ል​ንም ያስ​ተ​ሰ​ርይ፥ የዘ​ለ​ዓ​ለ​ም​ንም ጽድቅ ያገባ፥ ራእ​ይ​ንና ትን​ቢ​ትን ያትም፥ ቅዱሰ ቅዱ​ሳ​ኑ​ንም ይቀባ ዘንድ በሕ​ዝ​ብ​ህና በቅ​ድ​ስት ከተ​ማህ ላይ ሰባ ሱባዔ ተቀ​ጥ​ሮ​አል። 25ስለ​ዚህ ዕወቅ፤ አስ​ተ​ው​ልም፤ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን መጠ​ገ​ንና መሥ​ራት ትእ​ዛዙ ከሚ​ወ​ጣ​በት ጀምሮ እስከ ንጉሥ ክር​ስ​ቶስ ድረስ ሰባት ሱባ​ዔና ስድሳ ሁለት ሱባዔ ይሆ​ናል፤ ጎዳ​ና​ዋና ቅጥ​ርዋ ተመ​ልሶ ይሠ​ራል፤ ጊዜ​ውም ይፈ​ጸ​ማል።#ዕብ. “እር​ስ​ዋም በጭ​ንቅ ዘመን ከጎ​ዳ​ናና ከቅ​ጥር ጋር ትሠ​ራ​ለች” ይላል። 26ከስ​ድሳ ሁለት ሱባዔ በኋ​ላም መሢሕ ይገ​ደ​ላል፤ በእ​ር​ሱም ዘንድ ፍትሕ የለም፤ ከሚ​መ​ጣ​ውም አለቃ ጋር ከተ​ማ​ዪ​ቱ​ንና መቅ​ደ​ሱን ያጠ​ፋል፤ ፍጻ​ሜ​ውም በጎ​ርፍ ይሆ​ናል፤ እስከ መጨ​ረ​ሻም ድረስ ጦር​ነት ይሆ​ናል፤ ጥፋ​ትም ተቀ​ጥ​ሮ​አል። 27እር​ሱም ከብዙ ሰዎች ጋር ቃል ኪዳን ለአ​ንድ ሱባዔ ያጸ​ናል፤ በሱ​ባ​ዔ​ውም እኩ​ሌታ መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንና ቍር​ባ​ኑን ያስ​ቀ​ራል፤ በቤተ መቅ​ደ​ስም የጥ​ፋት ርኵ​ሰት ይሆ​ናል፤ እስከ ዘመ​ኑም ፍጻሜ የጥ​ፋት መጨ​ረሻ ይሆ​ናል።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ