መጽ​ሐፈ ተግ​ሣጽ 5

5
1 # በዕ​ብ​ራ​ይ​ስ​ጥና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ምሳሌ ምዕ. 29 ነው። አን​ገ​ቱን ካደ​ነ​ደነ ሰው ይልቅ፥
የሚ​ዘ​ልፍ ሰው ይሻ​ላል።
ድን​ገት ይቃ​ጠ​ላ​ልና፥ፈው​ስም የለ​ው​ምና።
2በጻ​ድ​ቃን መመ​ስ​ገን ሕዝ​ቦች ደስ ይላ​ቸ​ዋል፤
ክፉ​ዎች ገዢ​ዎች በሚ​ሆ​ኑ​በት ጊዜ ግን ሰዎች ያለ​ቅ​ሳሉ።
3ጥበ​ብን በሚ​ወ​ድድ ልጅ አባቱ ደስ ይለ​ዋል፤
ጋለ​ሞ​ቶ​ችን የሚ​ከ​ተል ግን ሀብ​ቱን ያጠ​ፋል።
4እው​ነ​ተኛ ንጉሥ ሀገ​ሩን ያጸ​ናል፤
ዐመ​ፀኛ ሰው ግን ያፈ​ር​ሰ​ዋል።
5በወ​ዳጁ ፊት ወጥ​መ​ድን የሚ​ያ​ዘ​ጋጅ ሰው
የራ​ሱን እግ​ሮች በው​ስጡ ያገ​ባል።
6በክፉ ሰው ዐመፃ ወጥ​መድ ይበ​ዛል፤
ኀጢ​አ​ተኛ ሰውም በታ​ላቅ ወጥ​መድ ይወ​ድ​ቃል፥#“ኀጢ​አ​ተኛ ሰውም በታ​ላቅ ወጥ​መድ ይወ​ድ​ቃል” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም።
ጻድቅ ግን በደ​ስ​ታና በሐ​ሴት ይኖ​ራል።
7ጻድቅ የድ​ሆ​ችን ፍርድ ይመ​ለ​ከ​ታል፤
ኃጥእ ግን ዕው​ቀ​ትን አያ​ስ​ተ​ው​ልም።
ለድ​ሃም ዕው​ቀት ያለው ልቡና የለ​ውም።
8ክፉ​ዎች ሰዎች ከተ​ማን ያቃ​ጥ​ላሉ፤
ጠቢ​ባን ግን ቍጣን ይመ​ል​ሳሉ።
9ጠቢብ ሰው ሕዝ​ብን ይገ​ዛል፥
ክፉ ሰው ግን ይቈ​ጣል፥ ይሥ​ቁ​በ​ታ​ልም፥
ነገር ግን አያ​ሳ​ዝ​ነ​ውም።
10ደምን ለማ​ፍ​ሰስ የሚ​ተ​ባ​በሩ ሰዎች ጻድ​ቁን ሰው ይጠ​ላሉ፥
ቅኖች ግን ነፍ​ሱን ይሻሉ።
11አላ​ዋቂ ሰው ቍጣ​ውን ሁሉ ያወ​ጣል፤
ጠቢብ ሰው ግን ድር​ሻ​ውን እንኳ በከ​ፊል ያስ​ቀ​ረ​ዋል።
12ንጉሥ ሐሰ​ተኛ ነገ​ርን ቢያ​ደ​ምጥ፥
በእ​ርሱ በታች ያሉት ሁሉ ዐመ​ፀ​ኞች ይሆ​ናሉ።
13አበ​ዳ​ሪና ተበ​ዳሪ በተ​ገ​ናኙ ጊዜ
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሁለ​ቱን በአ​ን​ድ​ነት ይጐ​በ​ኛ​ቸ​ዋል።
14ለድ​ሆች በእ​ው​ነት የሚ​ፈ​ርድ ንጉሥ፥
ዙፋኑ ለዘ​ለ​ዓ​ለም#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለም​ስ​ክር” ይላል። ይጸ​ናል።
15በት​ርና ተግ​ሣጽ ጥበ​ብን ይሰ​ጣሉ፤
ስሕ​ተ​ተኛ ብላ​ቴና ግን ቤተ ሰቦ​ቹን ያሳ​ፍ​ራል።
16ኃጥ​ኣን ሲበዙ ኀጢ​አት ትበ​ዛ​ለች፤
ጻድ​ቃን ግን በክ​ፉ​ዎች ውድ​ቀት ይፈ​ራሉ።
17ልጅ​ህን ቅጣ፥ ዕረ​ፍ​ት​ንም ይሰ​ጥ​ሃል፤
ለነ​ፍ​ስ​ህም ክብ​ርን ይሰ​ጣ​ታል።
18ለኀ​ጢ​አ​ተኛ ሕዝብ አስ​ተ​ማሪ የለ​ውም፤
ሕግን የሚ​ጠ​ብቅ ግን ብፁዕ ነው።
19ክፉ አገ​ል​ጋይ በቃል አይ​ገ​ሠ​ጽም፤
ቢያ​ውቅ እንኳ አይ​ታ​ዘ​ዝ​ምና።
20በቃሉ የሚ​ቸ​ኩ​ለ​ውን ሰው ብታይ፥
ከእ​ርሱ ይልቅ ለአ​ላ​ዋቂ ተስፋ እን​ዳለ ዕወቅ።
21ቸል​ተኛ ሰው ከሕ​ፃ​ን​ነቱ ጀምሮ አገ​ል​ጋይ ይሆ​ናል፤
በኋላ ግን ራሱን ያሳ​ዝ​ናል።
22ቍጡ ሰው ጠብን ይጭ​ራል፥
ወፈ​ፍ​ተኛ ሰውም ኀጢ​አ​ትን ያበ​ዛል።
23ትዕ​ቢት ሰውን ያዋ​ር​ደ​ዋል፥
ሕሊ​ና​ውን የሚ​ያ​ዋ​ር​ደ​ውን ሰው ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለክ​ብር ያቀ​ር​በ​ዋል።
24ከሌባ ጋር የሚ​ካ​ፈል ነፍ​ሱን ይጠ​ላል፤
መሐ​ላ​ንም ቢያ​ወ​ር​ዱ​ለት ይም​ላል፤ አይ​ና​ገ​ር​ምም።
25በመ​ፍ​ራ​ትና በማ​ፈር ሰው ይሰ​ነ​ካ​ከ​ላል፤
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ታ​መን ግን ደስ ይለ​ዋል።
የሰው ኀጢ​አቱ በደ​ለኛ ያሰ​ኘ​ዋል፥
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የታ​መነ ሰው ግን ይድ​ናል።
26ብዙ ሰዎች ለመ​ኳ​ን​ንት ፊት ይላ​ላ​ካሉ፤
የሰው ፍርዱ ግን ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ነው።
27እው​ነ​ተኛ ሰው በግ​ፈኛ ሰው ዘንድ የተ​ናቀ ነው፤
ቀና መን​ገ​ድም በኃ​ጥ​ኣን ዘንድ አስ​ጸ​ያፊ ነው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ