1
የዮሐንስ ወንጌል 6:35
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፥ “የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም፤ በእኔ የሚያምንም ለዘለዓለም አይጠማም።
Lee anya n'etiti ihe abụọ
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:35
2
የዮሐንስ ወንጌል 6:63
ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው፤ ሥጋ ግን አንዳች አይጠቅምም፤ ይህም እኔ የምነግራችሁ ቃል መንፈስ ነው፤ ሕይወትም ነው።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:63
3
የዮሐንስ ወንጌል 6:27
የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ለዘለዓለም ሕይወት ለሚኖር መብል ሥሩ እንጂ ለሚጠፋው መብል አይደለም፤ ይህን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና።”
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:27
4
የዮሐንስ ወንጌል 6:40
የአባቴ ፈቃዱ ይህ ነው፤ ወልድን አይቶ የሚያምንበት ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኝ ነው፤ እኔም በመጨረሻዪቱ ቀን አስነሣዋለሁ።”
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:40
5
የዮሐንስ ወንጌል 6:29
ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፥ “ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው ታምኑ ዘንድ ነው፤” አላቸው።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:29
6
የዮሐንስ ወንጌል 6:37
አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፤ ወደ እኔ የሚመጣውንም ከቶ ወደ ውጭ አላወጣውም።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:37
7
የዮሐንስ ወንጌል 6:68
ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ እንዲህ አለው፥ “አቤቱ፥ የዘለዓለም የሕይወት ቃል እያለህ ወደ ማን እንሄዳለን?
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:68
8
የዮሐንስ ወንጌል 6:51
“ከሰማይ የወረደ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ከዚህ እንጀራ የሚበላ ለዘለዓለም ይኖራል፤ ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው ይህ እንጀራ ሥጋዬ ነው።”
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:51
9
የዮሐንስ ወንጌል 6:44
የላከኝ አብ ካልሳበው በቀር ወደ እኔ መምጣትን የሚችል የለም፤ እኔም በመጨረሻዪቱ ቀን አስነሣዋለሁ።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:44
10
የዮሐንስ ወንጌል 6:33
የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድ፤ ለዓለምም ሕይወትን የሚሰጥ ነውና።”
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:33
11
የዮሐንስ ወንጌል 6:48
የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:48
12
የዮሐንስ ወንጌል 6:11-12
ጌታችን ኢየሱስም ያን እንጀራ ይዞ አመሰገነ፤ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው፤ ደቀ መዛሙርቱም ለተቀመጡት ሰዎች ሰጡአቸው፤ ከዓሣውም እንዲሁ የፈለጉትን ያህል ሰጡአቸው። ከጠገቡም በኋላ ደቀ መዛሙርቱን፥ “ከቍርስራሹ ምንም የሚወድቅ እንዳይኖር የተረፈውን ቍርስራሽ አንሡ፤” አላቸው።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:11-12
13
የዮሐንስ ወንጌል 6:19-20
ሃያ አምስት ወይም ሠላሳ ምዕራፍ ያህል ከሄዱ በኋላ ጌታችን ኢየሱስን በባሕር ላይ ሲሄድ አዩት፤ ወደ ታንኳዉ በቀረበ ጊዜም ፈሩ። እርሱም፥ “እኔ ነኝ፤ አትፍሩ” አላቸው።
Nyochaa የዮሐንስ ወንጌል 6:19-20
Ebe Mmepe Nke Mbụ Nke Ngwá
Akwụkwọ Nsọ
Atụmatụ Ihe Ogụgụ Gasị
Vidiyo Gasị