መዝሙር 118

118
መዝሙር 118
1 እግዚአብሔር ቸር ነውና አመስግኑ፤
ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።
2የእስራኤል ሕዝብ፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።
3የአሮን ቤት፣ “ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበል።
4 እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ፣
“ምሕረቱ ለዘላለም ነው” ይበሉ።
5በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤
እግዚአብሔርም መለሰልኝ፤ ከመጠበብም አወጣኝ።
6 እግዚአብሔር ከእኔ ጋራ ነው፤ አልፈራም፤
ሰው ምን ሊያደርገኝ ይችላል?
7ይረዳኝ ዘንድ እግዚአብሔር ከእኔ ጋራ ነው፤
የጠላቶቼንም ውድቀት አያለሁ።
8ሰውን መከታ ከማድረግ ይልቅ፣
እግዚአብሔር መታመን ይሻላል።
9በገዦች ተስፋ ከማድረግ ይልቅ፣
እግዚአብሔር መታመን ይሻላል።
10ሕዝቦች ሁሉ ከበቡኝ፤
ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።
11መክበቡንስ በየአቅጣጫው ከበቡኝ፤
ነገር ግን በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።
12እንደ ንብ መንጋ ከበቡኝ፤
ነገር ግን እንደሚነድድ እሾኽ ከሰሙ፤
በርግጥም በእግዚአብሔር ስም አስወግዳቸዋለሁ።
13ተገፍትሬ ልወድቅ ተንገደገድሁ፤
እግዚአብሔር ግን ረዳኝ።
14 እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤
አዳኝ ሆነልኝ።
15በጻድቃን ድንኳን የእልልታና የሆታ ድምፅ፣
እንዲህ እያለ ያስተጋባል፤
“የእግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች፤
16እግዚአብሔር ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አለች፤
እግዚአብሔር ቀኝ እጅ ብርቱ ሥራ ሠራች።”
17ተርፌ በሕይወት እኖራለሁ እንጂ አልሞትም፤
እግዚአብሔርንም ሥራ ገና እናገራለሁ።
18መገሠጹን እግዚአብሔር እጅግ ገሥጾኛል፤
ነገር ግን ለሞት አሳልፎ አልሰጠኝም።
19የጽድቅን ደጆች ክፈቱልኝ፤
በዚያ ገብቼ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ።
20ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤
ጻድቃን በርሷ በኩል ይገባሉ።
21ሰምተህ መልሰህልኛልና፣
አዳኝም ሆነህልኛልና አመሰግንሃለሁ።
22ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣
እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።
23 እግዚአብሔር ይህን አድርጓል፤
ይህም ለዐይናችን ድንቅ ነው።
24 እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤
በርሷ ሐሤት እናድርግ፤ ደስም ይበለን።
25 እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አድነን፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ እባክህ አሳካልን።
26እግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው።
እግዚአብሔር ቤት ባረክናችሁ።
27 እግዚአብሔር አምላክ ነው፤
ብርሃኑንም በላያችን አበራ፤
እስከ መሠዊያው#118፥27 ወይም የክብረ በዓልን መሥዋዕት በገመድ ማሰር ወይም መውሰድ ቀንዶች ድረስ በመውጣት፣
ዝንጣፊ ይዛችሁ በዓሉን ከሚያከብሩት ጋራ ተቀላቀሉ።
28አንተ አምላኬ ነህ፤ አመሰግንሃለሁ፤
አንተ አምላኬ ነህ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ።
29ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤
ፍቅሩም ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

Currently Selected:

መዝሙር 118: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ