መዝሙረ ዳዊት 127
127
1የዕርገት መዝሙር።
ጌታ ቤትን ካልሠራ፥
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፥
ጌታ ከተማን ካልጠበቀ፥
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።
2 #
መክ. 2፥24። እናንተ የመከራን እንጀራ የምትበሉ፥
ማለዳ መነሣታችሁ፥ አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው።
እርሱ ለሚወዱት እንቅልፍን ይሰጣልና።
3 #
መዝ. 115፥14፤ 128፥3፤ ዘዳ. 28፥11፤ ምሳ. 17፥6። እነሆ፥ ልጆች የጌታ ስጦታ ናቸው፥
የማሕጸንም ፍሬ የእርሱ ዋጋ ነው።
4በኃያል እጅ እንዳሉ ፍላጾች፥
የጐልማስነት ልጆች እንዲሁ ናቸው።
5ከእነርሱ ዘንድ ምኞቱን የሚፈጽም ሰው የታደለ ነው፥
ጠላቶቻቸውን በአደባባይ በተናገሩ ጊዜ እርሱ አያፍርም።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 127: መቅካእኤ
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ