1
የሉቃስ ወንጌል 21:36
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
እንግዲህ ከዚህ ከሚመጣው ሁሉ በጸሎታችሁ ማምለጥ እንድትችሉ፥ በሰው ልጅ ፊትም እንድትቆሙ ሁልጊዜ ትጉ።”
Thelekisa
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:36
2
የሉቃስ ወንጌል 21:34
“ራሳችሁን ጠብቁ፤ በመብልና በመጠጥ፥ በመቀማጠልና የዓለምን ኑሮ በማሰብ ልባችሁን አታደንድኑ፤ ያቺ ቀንም በድንገት ትደርስባችኋለች።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:34
3
የሉቃስ ወንጌል 21:19
በትዕግሥታችሁም ነፍሳችሁን ገንዘብ ታደርጓታላችሁ።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:19
4
የሉቃስ ወንጌል 21:15
በእናንተ ላይ የሚነሡ ሊመልሱላችሁና ሊከራከሯችሁ እንዳይችሉ እኔ አፍንና ጥበብን እሰጣችኋለሁ።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:15
5
የሉቃስ ወንጌል 21:33
ሰማይና ምድር ያልፋል፤ ቃሌ ግን አያልፍም።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:33
6
የሉቃስ ወንጌል 21:25-27
“በፀሐይና በጨረቃ፥ በከዋክብትም ላይ ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ይጨነቃሉ፤ ከባሕሩና ከሞገዱ ድምፅ የተነሣም ይሸበራሉ። በዓለም ላይ ከሚመጣው ፍርሀትና ሽብር የተነሣም የሰዎች ነፍስ ትዝላለች፤ ያንጊዜ የሰማያት ኀይል ይናወጣልና። ያንጊዜም በሰማይ ደመና፥ በፍጹም ኀይልና ክብር ሲመጣ የሰውን ልጅ ያዩታል።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:25-27
7
የሉቃስ ወንጌል 21:17
ሁሉም ስለ ስሜ ይጠሉአችኋል፤ ይገድሉአችኋልም።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:17
8
የሉቃስ ወንጌል 21:11
በየሀገሩ ታላቅ የምድር መነዋወጥና ራብ፥ በሰውም ላይ በሽታና ፍርሀት ይመጣል፤ በሰማይም ታላቅ ምልክት ይሆናል።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:11
9
የሉቃስ ወንጌል 21:9-10
ጦርነትንና ጠብን፥ ክርክርንም በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ አስቀድሞ ይህ ይሆን ዘንድ ግድ ነውና፤ ነገር ግን ወዲያው የሚፈጸም አይደለም።” እንዲህም አላቸው፥ “ሕዝብ በሕዝብ ላይ፥ ነገሥታትም በነገሥታት ላይ ይነሣሉ።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:9-10
10
የሉቃስ ወንጌል 21:25-26
“በፀሐይና በጨረቃ፥ በከዋክብትም ላይ ምልክት ይሆናል፤ በምድር ላይም አሕዛብ ይጨነቃሉ፤ ከባሕሩና ከሞገዱ ድምፅ የተነሣም ይሸበራሉ። በዓለም ላይ ከሚመጣው ፍርሀትና ሽብር የተነሣም የሰዎች ነፍስ ትዝላለች፤ ያንጊዜ የሰማያት ኀይል ይናወጣልና።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:25-26
11
የሉቃስ ወንጌል 21:10
እንዲህም አላቸው፥ “ሕዝብ በሕዝብ ላይ፥ ነገሥታትም በነገሥታት ላይ ይነሣሉ።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:10
12
የሉቃስ ወንጌል 21:8
እርሱም እንዲህ አላቸው፥ “ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ፤ ጊዜውም ደርሶአል እያሉ በስሜ ይመጣሉና እንዳያስቱአችሁ ተጠንቀቁ፤ እነርሱንም ተከትላችሁ አትሂዱ።
Phonononga የሉቃስ ወንጌል 21:8
Home
Bible
Plans
Videos