BibleProject | የዘወረደ ምልከታዎችናሙና
የምስራቹ የሚያሳየው የኢየሱስ መንፈስ በእርግጥም በሰው ልጆች ውስጥ እንደሚኖር፣ እንዲሁም ደግሞ መንፈሱ የእግዚአብሔርን የመገኘት ታላቅነት የሰው ልጆች እንዲለማመዱ ማድረግ እንደሚያስችል ነው። ሐዋሪያው ጳውሎስ ይህን ሚስጥር፣ "የክብር ተስፋ የሆነው በእናንተ ውስጥ ያለው ክርስቶስ" በማለት ገልፆታል።
ያንብቡ፦
ቈላስይስ 1÷25-29
ምልከታዎን ያስፍሩ፡
ይህን ክፍል ሲያጤኑ፣ የትኛዎቹ ቃላት ወይም ሀረጎች ጎልተው ይታይዎታል?
የኢየሱስ መንፈስ እርሱን በሚታመኑ ሰዎች ውስጥ መኖር የመቻሉን ሚስጥር ያሰላስሉ። ይህን እያሰላሰሉ ሳለ፣ ጥያቄዎችዎን፣ መደነቅዎን እና አግራምዎቶን ለእግዚአብሔር ወደሚቀርብ ጸሎት ይቀይሩት።
ቅዱሳት መጻሕፍት
ስለዚህ እቅድ
ባይብል ፕሮጀክት የዘወረደ ተከታታይ ትምህርቶችን ያዘጋጀው ግለሰቦች፣ ቡድኖች እንዲሁም ቤተሰቦች ዘወረደን፣ ማለትም የኢየሱስን ወደ ምድር መምጣት እንዲያከብሩ ለማነሳሳት ነው። ተስፋ፣ ሰላም፣ ሀሴት እና ፍቅር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጉማቸው ምን እንደሚመስል ተሳታፊዎች እንዲያጤኑ ለማገዝ እንዲጠቅም፣ ይህ የአራት ሳምንት የጥናት እቅድ የአኒሜሽን ቪዲዮዎችን፣ አጫጭር ማጠቃለያዎችን እና ሃሳብ ጫሪ ጥያቄዎችን አካቷል። እነዚህ አራት መንፈሳዊ እሴቶች እንዴት በኢየሱስ በኩል ወደ አለም እንደመጡ ለመረዳት፣ ይህን የጥናት እቅድ ይምረጡ።
More
ይህንን እቅድ ስላቀረበን BibleProject ን ማመስገን እንፈልጋለን። ለበለጠ መረጃ፣ እባክዎን ይጎብኙ፡- https://bibleproject.com/Amharic/